Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
በንገለ በከደና የመሰካበክ ዘጥጩድ ነጻ ሆባ ሀበባ የሷይጣን ሸንገላ መጽሐፍ አጋዥ ዲቪዲ የታዘለበት ጋፍጠህ ከማታውቀው በጣም ጠቃሚ ልበ ሙሉነት የምናገረው እኔ ስለ ጻፍኩት ሳይሆን ከርዕሰ ጉዳዩ የተነሣ ነው።ፖሥደረጋጳ ያዘሪገሪፖ ገጽ አንብብ ሁን ወደ ተግባር የምንገባበት ጊዜ ነው።
አጥምዶ የሚያውቅ ማንኛውም ሰው ወጥመዱ ከሁኔታቸው በግልጽ ይታወቃሉ እነርሱ ግን ያንን አይቀበሉም ጠላት እኛን ከሚያሳውርበት አደገኛ መንገድ አንዱ ራሳችን ላይ ብቻ እንድናተኩር ማድረግ ነው ይህ መጽሐፍ ያንን አደገኛ ወጥመድ ያጋልጣል እንዴት ከዚያ ማምለጥና ነጻ ሆነን መኖር እንደምንችል ያመለክታል ከመሰናከያ ነጻ መሆን ለማንኛውም ክርስቲያን አስፈላጊ ነው ምክንያቱም በዚህ ሕይወት እስካለን ድረስ መሰናከያ መምጣቱ እንደማይቀር ኢየሱስ ተናግሮአል ሉቃስ በአሜሪካ ባሉ አያሌ ቤተ ክርስቲያኖችና ይህን መልእክት በሰበክሁበት ሌሎች አገሮች ከሕዝቡ እጅ በላይ እንዲጸለይላቸው ወደ ፊት በመምጣት ምላሸ ይሰጣሉ ይህ በጣም ብዙ ቢሆንም ሁሉም ምላሽ ሰጥቷል ማለት ግን አይደለም አንዳንዶቹን ትዕቢት ምላሽ ከመስጠት ይይዛቸዋል ሰዎች ከዚህ ወጥመድ ሲፈቱ ሲፈወሱ ነጻ ሲወጡ በመንፈስ ቅዱስ ሲሞሉና ለጸሎታቸው መልስ ሲያገኙ ዐይቻለሁ ብዙ ጊዜ ነጻ ከሆኑ በኃላ በዚህ አጭር ጊዜ በቅጽበት የተቀበሉትን ለዓመታት ሲፈልጉ እንደ ነበር ይናገራሉ በሃያኛው መቶኛ ዓመታት የመጨረሻ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዕውቀት በጣም ጨምሯል ምንም እንኳ ዕውቀት ቢበዛም አሁንም በአማኞች በመሪዎችና በማኅበረ ምዕመኑ መካከል የበለጠ መከፋፈል ያለ ይመስላል ምክንያቱ ከእውነተኛ ፍቅር መጥፋት የተነሣ መሰናከያ መብዛቱ ነው ዕውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል ቆሮንቶስ መደበኛ የሕይወት መንገድ ነው ብለን እስክናስብ ድረስ ብዙዎች በዚህ አደገኛ ወጥመድ ተይዘዋል ይሁን እንጂ ክርስቶስ ከመመለሱ በፊት እውነተኛ አማኞች ከዚህ በፊት ከነበረው በተለየ ሁኔታ ይተባበራሉ ዛሬም ቢሆን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወንዶችና ሴቶች ከዚህ መሰናከያ ወጥመድ እንደሚፈቱ አምናለሁ መንፈሳዊ መነቃቃት አገሮችን ሲያዳርስ በማየት ረገድ ይህ ዋና ከሚባሉት ነገሮች አንዱ ነው ከዚህ በፊት እርሱን ለማየት ታውረው የነበሩ የማያምኑ ሰዎች በእኛ እርስ በርስ መዋደድ ኢየሱስን ይዩታል እንዲሁ ለመጻፍ ብቻ ተብሎ መጽሐፍ በመጻፍ አላምንም እግዚአብሔር ይህን መልእክት ልቤ ውስጥ አቀጣጥሎታል ዘላቂ ፍሬ ሲያስገኝም አይቻለሁ ይህን መልእክት ከተሰበክሁበት አንድ አገልግሎት በኃላ አንድ ፓስተር በአንድ ጊዜ ይህን ያህል ሰዎች ነጻ ሲሆኑ አይቼ አላውቅም ነበር ብሏሷል ይህ ግን የመጀመሪያው ብቻ መሆኑን እግዚአብሔር ለልቤ ተናግሮኛል ይህን መጽሐፍ ሲያነቡና መንፈስ ወደ ልባቸው ለሚያመጣው ጉትጐታ ሲታዘዙ ብዙዎች ነጻ ይሆናሉ ይፈወሳሉሌ እንደ ገና ይታደሳሉ በእነዚህ ገጾች ያሉ ቃሎችን ስታነቡ እውነተኛው መምህርና አጽናኝ በግል ለእናንተ ተግባራዊ እንደሚያደርጋቸው አምናለሁ እንደዚያ ሲያደርግ ይህ የተገለጠ ቃል ለሕይወታችሁና ለአገልግሎታችሁ ታላቅ ነጻነት ያመጣል እስቲ ማንበብ ከመጀመራችሁ በፊት እንጸልይ ምኙ ሪይ ይሀን መድሐፍ ዲያያያፖ ዲይ መንፈሰ ቃቋሆን ዳንድዮጥኝ ዳምንሃሥ ጳን። የእስራኤልን ልጆች አስቡ ከግብፅ ባርነት አውጥቶ ወደ ተስፋው ምድር እንዲያደርሳቸው እግዚአብሔር አዳኝ ልኮላቸው ነበር አንድ ዓመት በምድረ በዳ ከቆዩ በኃላ ምድሩን እንዲሰልሉ መሪዎች ተላኩ የተላኩት ግን እያጉረመረሙ ተመለሱ ከእነርሱ ይልቅ ግዙፎችና በሚሊታሪ ዐቅማቸው ጠንካሮች የነበሩትን በምድሩ የነበሩትን ሕዝብ ፈርተው ነበር ከኢያሱና ከካሌብ በቀር ሕዝቡ ሁሉ ከመሪዎቹ ጋር ተስማሙ ሕዝቡ እግዚአብሔር ከግብፅ ያወጣቸው ሊያጠፋቸው እንደ ሆነ አሰቡ በሙሴና በእግዚአብሔር ተሰናከሉ ይህ ሁኔታ ከአንድ ዓመት ለበለጠ ጊዜ ቀጥሎ ነበር በእነርሱ መሰናከል ያ ትውልድ እንደሚሰጣቸው እግዚአብሔር ቃል የገባላቸውን ምድር በፍጹም እንዳያዩ ተደረጉ በከፍተኛ ተነሳሽነት እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ የነበሩ ብዙዎች በክፉ ሰዎች ወይም በሥጋውያን ክርስቲያኖች በደል ስለ ደረሰባቸው በሕይወታቸው በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ገብተዋል እንደ እውነቱ ከሆነ እነዚህ ሰዎች በደል ተፈጽሞባቸዋል ይሁን እንጂ ይህ መሰናከል እግዚአብሔር ለሕይወታቸው ካለው ፈቃድ ለማውጣት ጠላት ያለውን ዓላማ ያስፈጽማል ከመሰናከል ራሳችሁን የምትጠብቁ ከሆነ በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ እንደ ሆናችሁ ትዘልቃላችሁ ከተሰናከላችሁ ግን የእርሱን ዓላማና ፈቃድ ለመፈጸም በምርኮ በጠላት ትወሰዳላችሁ ከመሰናከል ነጻ ሆኖ መኖር በጣም ጠቃሚ ነው እግዚአብሔር ሳያውቀው በእኛ ላይ ምንም ነገር እንደማይደርስ ማስታወስ ይኖርብናል እርሱ በፈለገ ጊዜ ሰይጣን እኛን ማጥፋት ቢችል ኖየሮ እርሱ የሰው ልጅን በጣም ስለሚጠላ ገና ዱሮ ጠራርጐ ያጠፋን ነበር ምንጊዜም ይህን ቃል አትርሱ በሰዎች ሁሉ ላይ ከደረሰው የተለየ ፈተና አልደረሰባቸሁም እግዚአብሔር ታማኝ ነው ስለዚህ ከምትችሉት በላይ አንድትፈተኑ አይተዋቸሁም ነገር ግን በምትፈተኑበት ጊዜ ፈተናውን መታገሥ አንድትችሉ መውጫ መንገዱን ያዘጋጅላችኃል ቆሮንቶስ መውጫ መንገዱን እንጂ ማምለጫ መንገዱን አለማለቱን ልብ አድርጉ የቱንም ያህል ትልቅ ወይም ትንሽ ቢሆን እኛ ላይ የሚደርሰውን ማንኛውንም ከባድ ሁኔታ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያውቀዋል ከዚያ መውጣት የምንችልበትንም መንገድ ያዘጋጃል እኛ በመታዘዝና ከመሰናከል ነጻ በመሆን ከጸናን የእግዚአብሔር ዕቅድ የተጨናገፈ መስሎ ቢታየን እንኳ እንዲያውም ዕቅዱ የሚፈጸምበት መንገድ ይሆናል ስለዚህ ይህን አስታውሱ ባለ መሰናከል ለእግዚአብሔር ተገዙ ዲያብሎስን ተቃወሙት እርሱም ከአናንተ ይሸሻል ያዕቆብ ሖቆ ዲያብሎስን የምንቃወመው ባለ መሰናከል ነው ሕልሙ ወይም ራእዩ እናንተ ካሰባችሁት በተለየ ሁኔታ ይፈጸም ይሆናል ይሁን እንጂ ቃሉና ተስፋው በፍጹም ሳይፈጸም አይቀርም ጭንገፋ የሚመጣው ባለ መታዘዝ ነው ሌላ ዓይነት ተላልፎ መሰጣጠት ብዙዎች እንደ ዮሴፍ በወንድሞቻቸው በደል አልደረሰባቸውም ያንን ያደረጉ ጠላቶቹ ቢሆኑ ኖሮ ይህን ያህል አያምም ነበር ያንን ያደረጉ ግን የሥጋና የደም ወንድሞቹ ነበሩ እርሱን ማበረታታት መደገፍ መከላከልና ለእርሱ ማሰብ የነበረባቸው እርሱ ነበሩ ዮሴፍ ላይ ከደረሰው የበለጠ በደል ይኖር ይሆን። እኔና ሚስቴ ወደ አሁን አገልግሎታችን ከመግባታችን በፊት ሰባት ዓመት ሙሉ የረዳትነት አገልግሎት ውስጥ ነበርኩ የወጣቶች ፓስተርም ነበርኩ የወጣቶች ፓስተር በነበርኩ ጊዜ እኔን ወይም የማቀርበውን መልእክት የማይወድ አንድ ሰው ነበር እንደ ማንኛውም ሰው ቢሆን ኖሮ ይህን ያህል አያሳስበኝም ነበር ይህ ሰው ግን እኔ ላይ ሥልጣን ያለው ሰው ነበር ለወጣቶች ጠንከር ያለ የንጽሕናና የቅድስና መልእክት እንዳቀርብ እግዚአብሔር ልቤ ውስጥ እንዳኖረ እምነት ነበረኝ የዚያ ሰው ልጅ ደግሞ እኔ የማስተምራቸው ወጣቶች ቡድን ውስጥ ነበር የዚህ ወጣት ልብ በመልእክቱ በጣም ተነካ አንድ ቀን ወደ እኛ መጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ እርሱም ሆነ ሌሎች ወጣቶች እንዲከተሉ ከማስተምረው አንጻር እቤቱ የሚያየው አኗኗር በጣም የወረደ መሆኑ ረብሾት ነበር ይህ ሁኔታና ሌሎች የሰብዕና ግጭቶች እኔን ከዚያ ማስወገድ እንዳለበት ያንን ሰው ወደ ውሳኔ አድርሶት ነበር ወደ ዋናው ፓስተር እየሄደ እኔ ላይ እንዲቆጣ የሐሰት ክሶች ያቀርብብኝ ነበር ከዚያም ወደ እኔ እየመጣ ዋናው ፓስተር እኔን በጣም እንደ ተቆጣና እርሱ ግን እኔን በመደገፍ እንደ ቆመ ይነግረኝ ነበር እኔ ፊት ፈገግተኛ ይሆናል ፍላጐቱ ግን እኔን ማጥፋት ነበር አንዳንድ ወጣቶች ወደ እኔ እየመጡ ከዚያ ቦታ ልባረር መሆኑን እንደ ሰሙ ይነግሩኝ ነበር ያንን ወሬ እያስፋፋ የነበረው የዚያ ሰው ልጅ ሲሆን ያንን የሚያደርገው እቤት የሰማውን መልሶ እያወራ እንጂ እኔን ለመጉዳት አልነበረም በጣም ተቆጣሁ ግራ ተጋባሁ ወደዚያ ሰው ሄጄ ለምን እንደዚያ እንደሚያደርግ ጠየቅሁት እርሱም እንደዚያ ማድረጉን ቢያምንም ራሱ የፈጠረው ሳይሆን የተናገረው ዋናው ፓስተር ሲል የሰማውን እንደ ሆነ ነገረኝ በዚህ ሁኔታ ወሮች አለፉ ሁኔታው ግን ምንም ዓይነት መሻሻል አያሳይም ነበር ሌላው ቀርቶ ያ ሰው በእኔና በዋናው ፓስተር መካከል የነበረ ግንኙነት እንኳ እንዲቋረጥ አደረገ እንዲህ የሚያደርገው እኔ ላይ ብቻ ሳይሆን እርሱ የማይፈልጋቸው ሌሎች ፓስተሮችም ላይ ነበር በዚያ ቤተ ክርስቲያን ማገልገሌን መቀጠል ወይም ማቋረጥ ያለብኝ መሆኑን ባለ ማወቃችን ቤተ ሰቤ ላይ ውጥረት ተፈጠረ አዲስ ቤት ገዝተን ነበር ሚስቴም እርጉዝ ነበረች በወቅቱ ምንም የምንሄድት ቦታ አልነበረንም ወደዚያ ቤተ ክርስቲያን የመራኝ እግዚአብሔር መሆኑን በጣም አምን ስለ ነበር እዚያው መቆየት እንጂ ጥሎ የመሄድ ዕቅድ አልነበረኝም ሜስቴ በሁኔታው በጣም አዝና ነበር ከአገልግሎት እንደሚያግዱህ አውቃለሁ ሁሉም የሚነግሩኝ ያንን ነው አለችኝ እነርሱ አልቀጠሩኝም እግዚአብሔር ካልፈቀደ እኔን ማባረር አይችሉም አልኳት እውነታውን ለመካድ እየሞከርኩ እንደ ሆነ ስላሰበች የዚያ ቤተ ክርስቲያን ሥራዬን እንዳቋርጥ አጥብቃ ለመነችኝ በመጨረሻ እኔን ለማሰናበት ውሳኔ የመደረጉ ወሬ ተሰማ በወጣቶቹ ቡድን ለውጥ መደረጉን ዋናው ፓስተር ለቤተ ክርስቲያኑ ሰዎች ተናገረ ያኔም ቢሆን እኔ ላይ ከሾመው ሰው ጋር ስለ ተፈጠረው አለ መግባባት ከእርሱ ጋር አልተነጋገርኩም ነበር ከእርሱና ከዚያ ሰው ጋር በሚቀጥለው ቀን እንድነጋገር ቀጠሮ ተያዘ ለራሴ በመከራከር ምንም እንዳልናገር እግዚአብሔር በጣም ግልጽ በሆነ ሁኔታ ልቤ ላይ አኑሮ ነበር በሚቀጥለው ቀን ከፓስተሩ ጋር ስገናኝ ብቻውን ቢሮ ውስጥ ሆኖ በማግኘቴ ገርሞኝ ነበር እኔን ፊት ለፊት እያዬ «ጆን ወደዚህ ቤተ ክርስቲያን የመራህ እግዚአብሔር ነው ትተኸን እንድትሄድ አልፈልግም አለ እፎይታ ተሰማኝ በመጨረሻው ሰዓት እግዚአብሔር ተከላከለልኝ ይኸ ሰውዬ የጠመደህ ለምንድነው። አልኩ ገና እንዲህ ሲል የእግዚአብሔር ሰላም ልቤን ሞላው በመገረም ራሴን ነቀነቅሁ ምንም ነገር እንዳደርግ እግዚአብሔር እንደማይፈልግ በጣም እርግጠኛ ሆንኩ ያንን ማስረጃ ቀዳድጄ ጣልኩ በኋላ ላይ ረጋ ብዬ ሁኔታውን ስመለከተው አገልግሎት ውስጥ ላለ ሌላ ሰው ከመከላከል የበለጠ እኔ ራሴ የመበቀል ፍላጐት እንደ ነበረኝ ተረድቻለሁ ዓላማዬ ራስ ወዳድነትን መሠረት ያደረገ አለመሆኑን እንደ ምክንያት በማቅረብ ራሴን አሳምፔዋለሁ እንደ እውነቱ ከሆነም የነበረኝ ማስረጃ ትክክል ነበር ዓላማዬ ግን ንጹሕ አልነበረም ጊዜ አለፈ አንድ ቀን ወደ ቢሮ ከመግቢያ ሰዓት በፊት ከቤተ ክርስቲያኑ ውጪ ሆፔ እየጸለይኩ እያለ ሰውየው በመኪና ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ አየሁ ወደ እርሱ ሄጄ ራሴን በፊቱ ዝቅ እንዳደርግ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ሐሳብ አመጣ ወዲያውኑ ለራሴ መከራከር ጀመርኩ ጌታ ሆይ እንደዚያማ አይሆንም ይህን ሁሉ ችግር የፈጠረ እርሱ ነው ወደ እኔ መምጣት ያለበት እርሱ እንጂ እኔ አይደለሁም መጸለይ ቀጠልኩ ይሁን እንጂ ወዲያውኑ ወደ እርሱ በመሄድ ራሴን በፊቱ ዝቅ እንዳደርግ እግዚአብሔር በድጋሚ አሳሰበኝ ያ ሐሳብ ከእግዚአብሔር እንደ ነበር ዐውቃለሁ ቢሮዬ ሆሄ ደወልኩለትና ወደ እርሱ ቢሮ ሄድኩ ሆኖም እግዚአብሔር ባይናገረኝ ኖሮ የተናገርኩትና የተናገርኩበት መንፈስ በጣም የተለየ ይሆን ነበር በፍጹም ቅንነት ይቅርታ እንዲያደርግልኝ ጠየቅሁት ነቅፌህ ነበር ከዚያም አልፎ ፈርጄብህ ነበር አልኩት እርሱም ወዲያውኑ ለስለስ አለ ለአንድ ሰዓት ያህል አወራን ምንም እንኳ በእርሱና በሌሎች ፓስተሮች መካከል የነበረው ችግር ቢቀጥልም ከዚያ ቀን ወዲህ እኔን ማጥቃቱን አቆመ ከስድስት ወር በኋላ ከአገር ውጪ እያገለገልኩ እያለ ይህ ሰው የፈጸመው በደል ሁሉ ለዋናው ፓስተር ተገለጠ ነገሩ ከአገልግሎቱ ሌሎች ገጽታዎች ጋር እንጂ ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም የሰውዬው በደል እኔ ከማውቀው የበለጠ ከባድ ነበር ወዲያውኑ ከቤተ ክርስቲያኑ ታገደ ውሎ አድሮ ፍርድ መጣ በእኔ እጅ ግን አልነበረም እኔ ላይ ማድረግ የፈለገው እርሱ ላይ ተደረገበት ይሁን እንጂ በሆነው ነገር አልተደሰትኩም ለእርሱና ለቤተ ሰቡ አዘንኩ በእርሱ በኩል የዚያ ዓይነት ችግር ደርሶብኝ ስለ ነበር ሕመሙ ይገባኛል ከስድስት ወር አስቀድሞ ይቅር ብዬው ስለ ነበር አሁን እርሱን መውደድ ችያለሁ እንዲህ ያለ ነገር እንዲደርስበት አልፈለግሁም ነበር ከአንድ ዓመት በፊት በእርሱ ላይ ቁጣ አድሮብኝ በነበረ ጊዜ ታግዶ ቢሆን ኖሮ ደስ ይለኝ ነበር ትሕትናና ራስን ዝቅ ማድረግ እኔ ራሴ ለመበቀል አለመፈለጌ ከበደል ወይም ከመሰናከል እስር ቤት ነጻ አውጥተውኛል ከአንድ ዓመት በኋላ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ አየሁት የእግዚአብሔር ፍቅር ውስጤ ነደደ እርሱ ወደ ነበረበት ሮጩ ሄድኩና አቀፍኩት ነገሮች ለእርሱ መልካም እንደ ነበሩ ሲነግረኝ ከልቤ ደስ አለኝ ከወሮች በፊት ቢሮው ሄጄ ራሴን ዝቅ ባላደርግ ማለትም ትሑት ሆፔ ባልሆን ኖሮ በዚያ ቀን ዐይኑን ማየት ይከብደኝ ነበር እርሱን ካየሁ አሁን ጥቂት ዓመታት አልፈዋል ግን ስለ እርሱ የሚሰማኝ ፍቅር ብቻ ነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ሆኖ እንዳየውም እውነተኛ ፍላጐት አለኝ እግዚአብሔር ራሱ ሳኦል ላይ ፈራጅ እንዲሆን በመምረጡ ዳዊት አስተዋይነቱን አሳይቷል ምናልባትም በሳኦል ላይ ለመፍረድ እግዚአብሔር የተጠቀመው በማን ነበር። ሳሙኤልን በዚያ ቦታ ያስቀመጠው እግዚአብሔር ነበር ለዔሊና ለልጆቹ ዐመፅ ተጠያቂ እርሱ እንዳልነበረ ያውቃል ከእነርሱ ሥልጣን ሥር የሆነው ሊያገለግላቸው እንጂ ሊፈርድባቸው እንዳይደለ ይረዳል ዔሊ የእግዚአብሔር እንጂ የእርሱ አገልጋይ አልነበረም የእርሱ በሆኑት ላይ ምን ማድረግ እንዳለበት እግዚአብሔር በሚገባ ያውቃል ልጆች አባቶችን አይገሥጹም ይልቁን ልጆችን ማስተማርና ማስተካከል የአባቶች ሥራ ነው እንድናስተምራቸው እግዚአብሔር የሰጠንን ሰዎች ማስተካከልና ማረም ተገቢ ነው ያ የእኛ ኃላፊነት ነው በእኛ ደረጃ ያሉትን እንደ ወንድሞችና እኅቶች ማበረታታትና መምከር አለብን በዚህና በመጨረሻው ምዕራፍ ግን እግዚአብሔር በእኛ ላይ ሥልጣን ለሰጣቸው ሰዎች የእኛ ምላሽ ምን መሆን እንዳለበት መናገር እፈልጋለሁ ሳሙኤል እግዚአብሔር የሾመውን መሪ በሚቻለው ሁሉ አገለገለ እንጂ እርሱ ላይ አልፈረደም እርሱን ለማረምም አልሞከረም ሳሙኤል የእርምት ቃል የተናገረው ባለፈው ሌሊት እግዚአብሔር ስለ ሰጠው ትንቢት እንዲነግረው ዔሊ በጠየቀው ጊዜ ብቻ ነበር ያኔም ቢሆን የተናገረው ከእግዚአብሔር የተቀበለውን እርምት እንጂ የራሱን አልነበረም ብዙዎች ይህን እውነት ይዘው ቢሆን ኖሮ የቤተ ክርስቲያኖቻችን ሁኔታ የተለየ ይሆን ነበር አብያተ ክርስቲያናት እንደ ፈለግን የምንገባባቸው የምንወጣባቸው አይደሉም በዚህ ዘመን ሰዎች አመራሩ ላይ አንዳች ስሕተት ከተመለከቱ በፍጥነት ቤተ ክርስቲያኖችን ለቅቀው ይሄዳሉ ምናልባት ፓስተሩ መባ ወይም ገንዘብ ለቤተ ክርስቲያኑ የሚሰበስብበትን መንገድ በተመለከተ አሠራሩ ላይ ሳይስማሙ ይችላሉ ገንዘቡ ጥቅም ላይ በሚውልበት ሁኔታ ጥያቄ ያድርባቸው ይሆናል በፓስተሩ ስብከት ካልተስማሙ ለቅቀው ይሄዳሉ ምናልባትም ፓስተሩ በቀላሉ ሊቀርቡት የማይቻልና የማይገኝ ወይም ደግሞ የትም የሚገኝ ተራ ዓይነት ሰው ይሆንባቸው ይሆናል ችግሩን በትዕግሥት ከመቀበልና በተስፋ ከመጠበቅ ይልቅ ችግር የሌለበት መስሎ ወደሚታያቸው ቦታ ይሮጣሉ ፍጹም የሆነ ፓስተር ወይም መጋቢ ኢየሱስ ብቻ ነው ታዲያ አንድ ችግር ሲፈጠር ቆም ብለን ከማሰብና መፍትሔውን ከመፈለግ ይልቅ ከችግሩ ሸሽተን ለማምለጥ የምንሞክረው ለምንድነው። መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር እንደ ወደደ እያንዳንዱን በቦታው መድቦአል ቆሮንቶስ ይላል እንጂ እያንዳንዱ አባል እንደ ወደደ ቤተ ክርስቲያን መቀያየር ይችላል አይልም እግዚአብሔር የሚፈልገው ቦታ ላይ ከሆናችሁ እናንተን ከዚያ ለማስወጣት ሰይጣን ሊያሰናክላችሁ እንደሚሞክር አትርሱ ወንዶችና ሴቶች ልጆችን እግዚአብሔር ከተከለበት ቦታ መንቀል ይፈልጋል እናንተን ከዚያ ከነቀለ ደግሞ ዓላማው በደንብ ይሳካለታል የቱንም ያህል ከባድ ችግር ቢኖር እንኳ ጸንታችሁ ከቆማችሁ ግን ዕቅዱን ታፈርሳላችሁ ከባድ መሳት ለአያሌ ዓመታት አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነበርኩ የዚያ ቤተ ክርስቲያን ፓስተር በአሜሪካ ከታወቁ ጥሩ ሰባኪዎች አንዱ ነበር መጀመሪያ የዚያን ቤተ ክርስቲያን ፕሮግራም ስካፈል ከአንደበቱ የሚፈልቀውን የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አፌን ከፍቼ ነበር የምሰማው ጊ ጊዜ እያለፈ ሄደ የእኔ ሥራ ድርሻ ፓስተሩን ማገልገል ስለ ነበር በጣም ከመቅረቤ የተነሣ አንዳንድ ደካማ ጐኖቹን ማየት ቻልኩ አገልግሎትን በተመለከተ በሚያሳልፋቸው አንዳንድ ውሳኔዎች ጥያቄ አደረብኝ ነቃፊና ፈራጅ ሆንኩ መሰናከል ወደ ሕይወቴ መጣ አሁንም እንደ ወትሮ ቢሰብክ እንኳ ከእግዚአብሔር የሆነ ነገር ወይም ቅባት አይሰማኝም ነበር ስብከቱ ለጥልቅ እኔነቴ አይደርስም ነበር የቅርብ ወዳጆቻችንና በቤተ ክርስቲያኑ ይሠሩ የነበሩ ባልና ሜስትም እኔን የተሰማኝ ዓይነት ስሜት ነበራቸው እነዚህ ሰዎች በእግዚአብሔር መሪነት የራሳቸውን አገልግሎት ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑን ለቅቀው መሄድ ነበረባቸው ከፈለግን አብረናቸው እንድንሄድ ጠይቀውን ነበር የገጠመንን ችግር በሚገባ ያውቁ ነበር እግዚአብሔር ለሕይወታችን ባለው ጥሪ መሠረት እንድንንቀሳቀስ ያበረታቱን ነበር ፓስተሩ ሚስቱና አመራሩ ያለባቸውን ችግር ሁሉ ይነግሩን ነበር ለእኔና ለአገልግሎቴ በጣም የሚያስቡ መስሎ ተሰምቶኝ ነበር ሆኖም ውይይታችን ቀድሞኑ የነበረንን ቅርታና መሰናከል ይበልጥ አቀጣጠለው እንጂ መፍትሔ አልሆነንም መጽሐፈ ምሳሌ ዕንጨት ከሌለ እሳት ይጠፋል አሾክሻኪ ከሌለም ጠብ ይበርዳል ይላል እነዚህ ወገኖች የነገሩን ነገር እውነት ሊሆን ይችላል ይሁን እንጂ በእኛም ሆነ በእነርሱ ውስጥ የመሰናከል እሳት እያቀጣጠለ በመሆነ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል አልነበረም አንተ የእግዚአብሔር ሰው መሆንህን በሚገባ እናውቃለን አሉኝ በዚህ ቦታ ይህ ሁሉ ችግር እየደረሰብህ ያለው በዚህ ምክንያት እንደ ሆነም አእንረዳለን እኔና ሜስቴ እነዚህ ሰዎች የተናገሩት ትክክል ነው ያለንበት ሁኔታ ጥሩ አይደለም ይህን ቤተ ክርስቲያን መልቀቅ አለብን ፓስተሩና ሚስቱ በጣም ስለሚወዱን ለእኛም ፓስተር ይሆኑናል ከእነርሱ ጋር ያሉት ሰዎችም እኛንም ሆነ እግዚአብሔር የሰጠንን አገልግሎት ይወዳሉ ተባባልን ቤተ ክርስቲያናችንን ለቅቀን በእነዚህ ባልና ሚስት ቤተ ክርስቲያን መካፈል ጀመርን ያ የዘለቀው ግን ለጥቂት ወሮች ብቻ ነበርኮ ከችግራችን ያመለጥን ቢመስለንም ግን አሁንም ቢሆን ትግል መኖሩን ተረዳን መንፈሳችን ውስጥ ደስታ አልነበረም የምናደርገው ሁሉ ነጻነት የሌለበትና የትግል ሆነብን ከመንፈስ ጋር አብረን መፍሰስ አልሆን አለን ይባስ ብሎ ደግሞ ከአዲሱ ፓስተርና ከሚስቱ ጋር የነበረን ግንኙነት እየሻከረ መጣ በመጨረሻ ትተነው ወደ መጣነው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናችን መመለስ እንዳለብን ዐወቅሁ ያንን ስናደርግ ከዚያ ይልቅ ሌላ ቦታ የበለጠ የምንወደድና ተቀባይነት የምናገኝ መስሎ ቢታየን እንኳ እዚያ በመገኘታችን በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ እንደ ሆንን ዐወቅን በኃላም አንድ ቀን እግዚአብሔርረ ጆን መጀመሪያውኑ ይህን ቤተ ክርስቲያን ለቅቀህ እንድትሄድ አልነገርኩህም ለቅቀህ የሄድከው ከመሰናከል የተነሣ ነው። የሚለው ነው የመጀመሪያው ልጄ ኤዲሰን የተወለደ ጊዜ ከሚስቴና ከእኔ በመገኘቱ ብቻ የእኛ ልጅ ሆኖአል ከሌሎች ሕፃናት ጋር ሕፃናት ማቆያ ቦታ የነበረ ጊዜ ባሕርዩን በማየት የእኔ ልጅ መሆኑን አትለዩም ወዳጆቻችንና ሌሎች ዘመዶቻችን ሊጐበኙን በመጡ ጊዜ አልጋው ላይ የታሰረውን ስሙን ስላዩ እንጂ ለይተው ሊያውቁት አልቻሉም ነበር ከሌሎች የተለየ የሚያደርገው ምንም ነገር አልነበረም ከጆንና ሊዛ ቢቭሬ በመወለዱ ብቻ ኤዲሰን የእነርሱ ልጅ ሆኖአል ሮሜ ላይ ጥቅም ላይ የዋለው ቴክኖን ነው የልጅነትን መንፈስ ስለ ተቀበልን የእግዚአብሔር ልጆች ቴክኖን መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ሆኖ ይመሰክርልናል ይላል አንድ ሰው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ጌታው አድርጐ ሲቀበል በአዲስ ልደት ልምምድ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል ዮሐንስ ይመ አዲስ ኪዳን ውስጥ ሷጂጅሯ ተብሎ የተተረጐመ ሌላው ቃል ሁዮስ ነው ብዙውን ጊዜ አዲስ ኪዳን ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለው የወላጆቹ ባሕርይ ወይም ባሕርያት ስላሉት የእነርሱ ልጅ መሆኑ የሚታወቅ የሚለው ነው ልጄ ኤዲሰን እያደገ ሲመጣ በመልክና በተግባር አባቱን መምሰል ጀመረ ኤዲሰን የስድስት ዓመት ልጅ እያለ እኔና ሊዛ ጉዞ ለማድረግ ወላጆቼ ጋ አኑረነው ነበር ከጉዞ ስንመለስ ኤዲሰን ቁርጥ አባቱን ነው የሚመስለው በማለት እናቴ ለሊዛ ነገረቻት ባሕርዩ እኔ በእርሱ ዕድሜ በነበርኩ ጊዜ የነበረኝ ዓይነት ነበር እያደገ ሲመጣ ደግሞ ይበልጥ እኔን እየመሰለ መጣ በአሁኑ ጊዜ በመወለዱ ብቻ ሳይሆን የአባቱ ዐይነት ባሕርይና ሰብዕና ያለው በመሆኑም ጭምር ማንም የጆን ቢቭሬ ልጅ መሆኑን ያውቃል ስለዚህ በቀላል ሁኔታ ለማስቀመጥ ቴክኖን የተሰኘው የግሪክ ቃል ጨቅላ ሕፃናት ማለት ሲሆን ሁዩስ የተሰኘው ቃል ግን ያደጉ ልጆችን ለመግለጽ ጥቅም ላይ ይውላል ማለት ነው እንደ ገና ሮሜ ስንመለከት በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ሁዩስ ናቸውና ነው የሚለው በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩት ያደጉና በሳሎች ልጆች መሆናቸውን በግልጽ ማየት እንችላለን ያላደጉና በሳል ያልሆኑ ክርስቲያኖች የእግዚአብሔርን መንፈስ ምሪት የሚከተሉት በጣም አልፎ አልፎ ነው ለሚገጥሟቸው ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ ምላሽ የሚሰጡት ስሜትን ወይም አእምሮን መሠረት በማድረግ ነው ለእግዚአብሔር መንፈስ ምሪት ብቻ ምላሽ መስጠት ገና አልተማሩም ኤዲሰን እያደገ ሲሄድ በባሕርይም አእየጐለመሰ ይሄዳል የበለጠ ባደገና በሳል በሆነ መጠን እኔም የበለጠ ኃላፊነት እሰጠዋለሁ አለማደጉና በሕፃንነት ባሕርይ ተወስኖ መቅረቱ በምንም ዐይነት ትክክል አይሆንም ሕፃን ሆነን እንድንቀር የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም የልጄ የኤዲሰን ባሕርይ እያደገና እየዳበረ የመጣበት አንዱ መንገድ አዳጋች ሁኔታዎችን በመጋፈጥ ነበር ትምህርት ቤት መሄድ በጀመረ ጊዜ አንዳንድ ጉልበተኛ ልጆች አጋጥመውት ነበር እነዚያ መጥፎ ልጆች ልጄ ላይ እያደረጉና እየተናገሩ ስለ ነበረው ነገር ሰማሁ ሄጄ ችግሩን ለመፍታት ፈልጌ ነበር ያ ግን ትክክል እንዳልሆነ ይገባኛል የእኔ ጣልቃ መግባት የኤዲሰንን ባሕርይ ዕድገት ሊያሰናክል ይችላል ስለሆነም እኔና ሚስቴ እቤት ውስጥ ለእርሱ ምክር መስጠትና ትምህርት ቤት ውስጥ እየገጠመው ላለው ችግር እርሱን ማዘጋጀት ቀጠልን በዚህ ችግር መሐል ለእኛ ምክር በመታዘዝ በባሕርይ መጐልመስና ማደግ ጀመረ እግዚአብሔር እኛን በተመለከተ የሚያደርገውም ይህንኑ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ሲናገር ያላሟግዳጩሌረሪ ልድ ዕሥጋ ፈያፖኃም ያታፇሐው መዕያራ መታሃ ፖታማሪ ይላል ዕብራውያን አካላዊ ዕድገት የጊዜ ጉዳይ ነው ማንኛውም የሁለት ዓመት ልጅ ቁመት ስድስት ጫማ አይሆንም አእምሮአዊ ዕድገት የመማር ጉዳይ ነው መንፈሳዊ ዕድገት ግን የጊዜም ሆነ የመማር ጉዳይ ሳይሆን የመታዘዝ ጉዳይ ነው እስቲ ሴጥሮስ የሚናገረውን እንስማ እንግዲህ ከርስቶስ በሥጋው መከራን ስለ ተቀበለ እናንተም በዚሁ ዓላማ ታጥቃችሁ ተነሠ ምከንያቱም በሥጋው መከራን የሚቀበል ሰው ኃጢአትን ትቶአል ጴጥሮስ ኃጢአትን የተወ ሰው ፍጹም ታዛዥ የእግዚአብሔር ልጅ ነው አድጐአል በሳል ሆኖአል የራሱን ሳይሆን የእግዚአብሔርን መንገድ ይከተላል ከተቀበለው መከራ የተነሣ ኢየሱስ መታዘዝን እንደ ተማረ ሁሉ እኛም ከሚገጥሙን አዳጋች ሁኔታዎች የተነሣ መታዘዝን እንማራለን በመንፈስ ቅዱስ የተነገረውን የእግዚአብሔር ቃል ስንሰማ በመከራና በችግር ጊዜ እናድጋለን በሳሎች እንሆናለን ቁልፉ የቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀታችን ሳይሆን መታዘዝ ነው አንዳንድ ሰዎች ለሃያ ዓመታት ክርስቲያኖች ቢሆኑም ከመጽሐፍ ቅዱስ እየጠቀሱ ቢናገሩም በሺዎች የሚቆጠሩ ስብከቶች ቢሰሙም ብዙ መጻሕፍት ቢያነቡም አሁንም መንፈሳዊ ቅዘን ጨርቅ የሚያስፈልጋቸው ለምን እንደ ሆነ አሁን አንዱን ምክንያት ተረድተናል እንዲህ ያሉ ወገኖች አዳጋች ሁኔታ በገጠማቸው ጊዜ ሁሉ በእግዚአብሔር መንፈስ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በራሳቸው መንገድ ለራሳቸው መከላከል ይፈልጋሉ ሁልጊዜ ይማራሉ ነገር ግን እውነትን ወደ ማወቅ ፈጽሞ ሊደርሱ አይችሉም ኛ ጢሞቴዎስ በሕይወታቸው ተግባር ላይ ስለማያውሉት እውነትን ወደ ማወቅ አይደርሱም እንድናድግና በሳሎች እንድንሆን ከተፈለገ እውነት በሕይወታችን የራሱን መንገድ መፈጸም አለበት መታዘዝ በሌለበት ሁኔታ በአእምሮ እውነትን መቀበል ብቻ በቂ አይደለም እየተማርን ቢሆን እንኳ ካለ መታዘዝ የተነሣ ሳናድግና በሳሎች ሳንሆን እንቀራለን ለራስ መጠንቀቅ ባለ መታዘዝ ውስጥ ያሉ ሰዎች ለራሳቸው የሚጠነቀቁበት በጣም የተለመደ ሰበብ የደረሰባቸው መሰናክል ወይም በደል ነው ያለፈ ጊዜ በደልን ማስተናገድ ሐሰተኛ ለራስ የመጠንቀቅ ስሜት ይፈጥራል ችግሩን ሌላው ሰው ላይ ስለምታደርጉት የራሳችሁን ደካማነት ከማየት ያግዳችኃል በድሎናል የምትሉትን ሰው ጥፋት ብቻ ስለምታዩ የራሳችሁን አለመብሰል ወይም ኃጢአት ማየት አትችሉም ስለዚህም በገጠማችሁ ችግር አማካይነት መልካም ባሕርይ እንድታዳብሩ እግዚአብሔር በሕይወታችሁ እየሠራ ያለውን ሳትቀበሉ ትቀራላችሁ የተሰናከለ ሰው የችግሩ ምክንያት ነው የሚለውን ነገር ቶሎ ያስወግዳል የኃላ ኃላም ከሰው ሁሉ ይርቅና መንፈሳዊ ከርታታ ይሆናል በቅርቡ አንዲት ሴት አንዱን ቤተ ክርስቲያን ትታ ወደ ሌላ ቤተ ክርስቲያን እየሄደች ስለ ነበረች ጓደኛዋ ነግራኝ ነበር አንድ ቀን አብረው ራት እንዲበሉ አዲሱን ፓስተር ወደ ቤቷ ጠርታው ነበር እየተጨዋወቱ እያለ ፓስተሩ የበፊቱ ቤተ ክርስቲያኗን የተወችው ለምን እንደ ነበር ይጠይቃታል ሴትዬዋም በበፊቱ ቤተ ክርስቲያን አመራር የነበረውን ችግር ትነግረዋለች ፓስተሩ በሚገባ ካደመጣት በኃላ ሁሉም ነገር እንደሚስተካከል ይነግራታል ከልምድ እንደ ተማርኩት ሴትየዋ ጉዳትና ነቃፊ ዝንባሌዋን በእግዚአብሔር ቃል መሠረት እንድትፈታ ቢነግራት ኖሮ በጣም የተሻለ ይሆን ነበር አስፈላጊ ከሆነም እግዚአብሔር ያንን ቤተ ክርስቲያን እንድትተው እስኪመራት ድረስ ወደ በፊቱ ቤተ ክርስቲያንዋ እንድትመለስ ሊነግራት ይገባ ነበር እግዚአብሔር በሰላም ካሰናበታችሁ ከዚያ መሄዳችሁ ትክክል መሆኑን ለሌሎች የማስረዳት ችግር አይገጥማችሁም የበፊቱ ቤተ ክርስቲያናችሁ ላይ የመፍረድ የመንቀፍ ወይም ችግሩን የማጋለጥ ዝንባሌ አይሰማችሁም ያቺ ሴት ብዙም ሳትቆይ ለአዲሱ ፓስተርና የመሪነት ችሎታው የሚኖራት አመለካከት ለበፊቱ ቤተ ክርስቲያን የነበራት አመለካከት ዓይነት እንደሚሆን አውቃለሁ ልባችሁ ውስጥ በደል ወይም መሰናከል ካለ ማንኛውንም ነገር የምታዩት ወይም የምትቀበሉት ከዚያ አንጻር ይሆናል ከእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ጋር የሚስማማ አንድ የዱሮ ምሳሌ አለ በዱሮ ጊዜ ሰፋሪዎች ወደ ምዕራቡ የአገሪቱ ክፍል በመጓዝ ላይ እያሉ አንድ አስተዋይ ሰው በአዲሱ ሰፈር ያለ ኮረብታ ላይ ቆሞ ይጠብቃቸዋል ከምሥራቅ የመጡት ሰፋሪዎች እዚያ ከመስፈራቸው በፊት ያገኙት የመጀመሪያ ሰው ይህን አስተዋይ ሰው ነበር እነርሱም የዚያ አካባቢ ሰዎች ምን ዓይነት እንደ ሆኑ በመጓጓት ጠየቁት የመለሰላቸው ትታችሁ በመጣችሁት ቦታ ያሉ ሰዎች ምን ዓይነት ናቸው። በቀጥታ ከእግዚአብሔር መስማት የሚሜፈልግ ሰው ነበር ኢየሱስን በተመለከተ በመለኮታዊ መገለጥ የተገኘ ይህ ዕውቀት መንፈሳዊ ነገርን የተራበ በመሆኑ ያገኘው ስጦታ ማለትም ልቡ ውስጥ ከበራለት ብርሃን የተቀበለው እንጂ ከራሱ ስሜት የፈለቀ አልነበረም ጴጥሮስ ያየውንና የሰማውን ብዙዎችም ዐይተውና ሰምተው ነበር ይሁን እንጂ እንደ ጴጥሮስ ልባቸው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ የተራበ አልነበረም አንደኛ ዮሐንስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በውስጣችሁ ይኖራልና ማንም እንዲያስተምራችሁ አያስፈልግም ነገር ግን እውነት እንጂ ሐሰት ያልሆነው የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉም ነገር እንደሚያስተምራችሁ ያም እውነት እንጂ ሐሰት እንዳልሆነ ይላል ይህ ቅባት ስምዖን ጴጥሮስን እያስተማረው ነበር ጴጥሮስ ሌሎች የሚሉትን ሁሉ ሰምቶ ነበር ይሁን እንጂ እግዚአብሔር የገለጠለትን ለመረዳት ውስጡን ተመለከተ ከእግዚአብሔር የሆነ እውነት ከተገለጠላችሁ ማንም ሊያናውጣችሁ አይችልም እግዚአብሔር ለእናንተ አንድ ነገር ከገለጠላችሁ ዓለም በሙሉ የሚናገረው ደንታ አይሰጣችሁም በልባችሁ ያለውን ማንም መለወጥ አይችልም ከዚያም ኢየሱስ አንተ ጴጥሮስ ነህ በዚህ ዐለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ የገሃነም ደጆችም አያሸንፏትም በማለት ለጴጥሮስና ለተቀሩት ደቀ መዛሙርት ተናገረ ማቴዎስ ስለሆነም የተገለጠው የእግዚአብሔር ቃል ጽኑ መሠረት መሆኑን በግልጽ እናያለን እዚህ ላይ ግን ጽኑ መሠረት የሆነው ጵጥሮስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መረዳቱ ነበር አብርሆት ያለው ቃል ከማቀርበው ስብከት የእግዚአብሔርን ድምፅ እንዲሰሙ ብዙ ጊዜ ለጉባኤዎችና ለግለ ሰቦች እናገራለሁ ብዙ ጊዜ ማስታወሻ መያዝ ላይ ስለምናተኩር የተነገረውን ሁሉ በጽሑፍ እናሰፍራለን እንዲህ ማድረጉ ቅዱሳት መጻሕፍትንና አተረጓጐማቸውን በተመለከተ ምናልባት የአእምሮ መረዳት ማለትም የጭንቅላት ዕውቀት ይሰጠን ይሆናል የሚኖረን የጭንቅላት ዕውቀት ብቻ ከሆነ ሁለት ነገሮች ሊሆኑ ይችላሉ በቀላሉ ለስሜታዊነት እንጋለጣለን ወይም በአእምሮ መረዳት በምንችለው ብቻ እንወሰናለን ይህ ግን ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያኑን የሚመሠርትበት ጽኑ መሠረት አይደለም ቤተ ክርስቲያኑ በቃል በተጠና ጥቅስ ብዛት ሳይሆን ከመለኮታዊ መገለጥ በተገኘ የእግዚአብሔር ቃል እንደምትመሠረት ነው እርሱ የተናገረው አንድ ስብከት ስንሰማ ወይም አንድ መጽሐፍ ስናነብ መንፈሳችን ውስጥ አብርሆት የሚያመጡ ቃሎች ወይም ሐረጐች መፈለግ አለብን ይህ ለእኛ የተገለጠ የእግዚአብሔር ቃል ነው የሚሆነው ብርሃንና መንፈሳዊ መረዳት ወይም ግንዛቤ ይሰጠናል ዘማሪው የቃልህ ትርጓሜ ያበራል አላዋቂዎችንም አስተዋዮች ያደርጋልዑ ይላል መዝሙር የሚያበራልንና ግልጽ የሚያደርግልን ቃሉ ለልባችን እንጂ ለአእምሮአችን የሚሰጠው ትርጓሜ አይደለም አንዳንዴ ሰባኪው እየተናገረ ያለው ስለ አንድ ርዕሰ ጉዳይ ቢሆንም እግዚአብሔር ለልቤ የሚሰጠው አብርሆት ግን ፍጹም የተለየ ሊሆን ይችላል አንዳንዴ ደግሞ አገልጋዩ የተናገረውን ቃል ራሱን ይቀባና ልቤ ውስጥ እንዲቀጣጠል ያደርጋል በዚህም ሆነ በዚያ ለእኔ የተገለጠ የእግዚአብሔር ቃል ሆኖአል ማለት ነው አላዋቂ መረዳት የሌለው ከመሆን ወደ በሳልነት አብሮሆት ያለው የሚለውጠን ይህ ነው እንግዲህ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያኑን እንደሚመሠርት የተናገረው በእንዲህ ዐይነቱ ልባችን ውስጥ አብርሆት በሚያገኝ ቃል ጽኑ መሠረት ነው ማለት ነው የተገለጠ የእግዚአብሔርን ቃል ኢየሱስ ከዐለት ጋር አመሳስሎታል ዐለት ጽናትና ብርታትን ይወክላል አንደኛው ዐለት ላይ ሌላው ደግሞ አሸዋ ላይ ተሠርተው ስለ ነበሩ ሁለት ቤቶች የተነገረውን ምሳሌ እናስታውሳለን ስደትን መከራንና ችግርን የመሳሰሉ አዳጋች ሁኔታዎች ሁለቱንም ቤቶች እንደ ማዕበል ሲመቷቸው ዐለት ላይ የተሠራው ቤት ጸንቶ ሲቆም አሸዋ ላይ የተሠራው ግን ሙሉ በሙሉ ፈረሰ ከእግዚአብሔር መስማት ያለብን አንዳንድ ነገሮች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አይገኙም ለምሳሌ ያህል ማንን ነው ማግባት ያለብኝ። የሚሉ ጥያቄዎች ይነሣሉ የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ማረጋገጥ ነበረብኝ አሁን ግን ወጥመድ ውስጥ ያለሁ ያህል ይሰማኛል ያኔ ልባችሁ ይዝላል ጋብቻችሁ ላይ የሚቃጣውን ችግር መቋቋም አትችሉም በነገራችሁ ሁሉ የምታወሳውሉና የምታመነቱ ትሆናላችሁ ከዚያም ሁለቱንም አሰናበትኳቸው ጋብቻን በተመለከተ ከእንግዲህ የምንገናኝበት ምክንያት እንደሌለም ነገርኳቸው እርሱ እፎይ ያለ ይመስል ነበር እርሷ ግን በጣም ተረብሻ ነበር ለቀጣዮቹ ሁለት ሳምንቶች ቢሮዋችን ውስጥ የነበረው ሁኔታ ጥሩ አልነበረም ሆኖም የተናገርኩት እውነት መሆኑን ዐውቅ ነበር ያ ወጣት የእርሷ ባል እንደሚሜሚሆን በእውነት እግዚአብሔር ተናግሮአት ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ለእርሱም ግልጽ እንደሚያደርግለት መተማመን ነበረባት ያ ሆኖ ቢሆን ኖሮ በእኔም ሆነ በእግዚአብሔር ቅር መሰኘት አይኖርም ነበር በነገሩ ገፍታ ከመሄድ እንድትቆጠብና እርሱም ከእግዚአብሔር እስኪሰማ ጊዜ ልትሰጠው እንደሚገባ ነገርኳት የነገርኳትንም አደረገች ሦስት ሳምንት ካለፈ በኃላ እንደ ገና እንዳናግራቸው ጠየቁኝ ወዲያውኑ የደስታ ስሜት ተሰማኝ በቀጠሮው ጊዜ ወደ ቢሮዬ ሲመጡ የእርሱ ዓይኖች እንደ ፈርጥ እያበሩ የወደ ፊት ሚሜስቴ እንድትሆን ይህችን ልጃገረድ እግዚአብሔር እንደ ሰጠኝ አሁን በጣም እርግጠኛ ሆፔአለሁ አለ በሰባት ወሮች ውስጥ ተጋቡ እግዚአብሔር አንድ ግንኙነት ወይም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዳኖራችሁ የምታውቁ ከሆነ ጠላት በቀላሉ እናንተን ከዚያ ማውጣት አይችልም በተገለጠ የእግዚአብሔር ቃልና ፈቃድ ላይ ተመሥርታችኃል ስለሆነም የማይቻል ቢመስል እንኳ በግጭቶች መካከል በሰላም ታልፋላችሁ ሌላ አማራጭ የለም የእኔና የሚስቴ የመጀመሪያዎቹ አምስት የትዳር ዓመቶች በጣም አስቸጋሪ ነበሩ ቀድሞ የነበረንን ፍቅር ማደስ የማይቻል እስኪመስል ድረስ እርስ በርስ እንነታረክ ነበር በዚያ ሁሉ መሐል በአንድነት ያቆየን አንድ ነገር ብቻ ነበር የተጋባነው በእግዚአብሔር ፈቃድ መሠረት እንደ ነበር ሁለታችንም በሚገባ እናውቅ ነበር ስለሆነም መፋታትን እንደ አንድ ምርጫ አልወሰድንም የነበረን ምርጫ እርሱ እንደሚፈውሰንና እንደሚለውጠን ማመን ብቻ ነበር የቱንም ያህል የሚያምም ቢሆን እንኳ ሁለታችንም በዚህ ሂደት ማለፍ ነበረብን ነገሩን ሁሉ እርግፍ አድርጌ ለመተው ባሰብኩ ጊዜ ሁሉ ትዳራችንን በተመለከተ እግዚአብሔር የሰጠንን ተስፋ ቃል አስታውስ ነበር ለአብሮነታችን እግዚአብሔር ያቀደውንና እያደረገ ያለውን ማጨናገፍ አልፈለግሁም እግዚአብሔር የሰጠን አንዱ ተስፋ ቃል እኔና ሚስቴ አንድ ላይ ሆነን እንደምናገለግለው ነበር ተስፋውን በሰጠን ጊዜ ያንን በቀላሉ ማየት ይቻላል ለአገልግሎት የሚያነሣሣ የእግዚአብሔር እጅ በሁለታችንም ላይ ነው በማለት አስቤ ነበር ትዳራችን ማዕበል መካከል ሲሆን ግን የተስፋ ቃሉ ግልጽ ሆኖ አልታየኝም ነበር ያም ሆኖ ግን ተስፋ መቁረጥ አልፈለግሁም ትዳራችን ውስጥ ከገባው ፀብና ትዕቢት የተነሣ ተፈጥሮአዊው ተስፋ እንኳ ጠፍቶ ነበር ይሁን እንጂ ያኔም ቢሆን ልቤ ውስጥ ልዕለ ተፈጥሮአዊው የሕይወት ዘር ነበር ያ ተስፋ በሚያስፈልገኝ ጊዜ መልሕቅ ወይም መሠረት ሆኖኝ ነበር ጊዜ እያለፈ ሲሄድ እግዚአብሔር ግንኙነታችንን መፈወሱ ብቻ ሳይሆን ቀድሞ ከነበረው የበለጠ መጽናት መጠንከሩ ግልጽ መሆን ጀሠመረ እርስ በርስ ይቅር በመባባልና ካለፈ ጥፋት በመማር በግጭቶች መሐል ተያይዘን አደግን አሁን ሁለታችንም አብረን እያገለገልን ነው ከእንግዲህ ሚስቴን እንደ ወዳጄና ምርጥ ጓደኛዬ ብቻ ሳይሆን በጣም የምተማመንባት አገልጋይ አድርጌ ነው የምመለከታት ከማንኛውም ሰው ይልቅ ምስጢሬን የማካፍለው ለእርሷ ነው እነዚያን አስቸጋሪ አምስት ዓመቶች ካሳለፍኩ በኃላ እግዚአብሔር በሁለታችንም ውስጥ ያለውን ደካማነት ዐይቶ እንደ ነበርና እርስ በርስ የነበረን የሻከረ ግንኙነት ያንን ወደ ብርሃን እንዳወጣው እረዳለሁ እንደ ባልና ሚስት አብረን መሆናችን ምን ያህል መልካም መሆኑን ሳስብ በጣም እደነቃለሁ ከሊዛ ጋር ከመተዋወቄ በፊት እግዚአብሔር ሚስት እንዲሰጠኝ አጥብቄ ስጸልይ ነበር ያ ምርጫ በሕይወቴ ካደረግሁት በጣም ጠቃሚ ውሳኔ ማለትም ለወንጌል ከመታዘዝ ቀጥሎ ሁለተኛው ነው እየጸለይኩና እግዚአብሔር ለሚስትነት የሚመርጥልኝን ሴት እየጠበቅሁ ስለ ነበር ሌሎች በትዳር ውስጥ የገጠማቸው ዐይነት ችግር እኔን እንደማይገጥመኝ አስብ ነበር ምንኛ ተሳስቻለሁ። እግዚአብሔር የመረጠልኝ ሚስት ልቤ በጣም የሚፈልጋትን ነበር ይሁን እንጂ እኔ ውስጥ የነበረውን ራስ ወዳድነትና አለመብሰል እንዲጋለጥ አድርጋ ነበር ከዚያም ያለፈ ብዙ ነገር ነበር ፍቺን በመምረጥ ወይም እርሷን በደለኛ በማድረግ ከግጭት ባመልጥ ኖሮ የእኔ ጮርቃነት አይጋለጥም ነበር በደል ደርሶብኛል በሚል ሽፋን እንደ ተሸፈነ ይቀር ነበር ጋብቻን በተመለከተ የእግዚአብሔርን ቃል ማወቄ እርሷን ትቼ ከመሄድ ጠብቆኛል ምናልባትም ይህን በማንበብ ላይ ያላችሁ አንዳንዶቻችሁ ትዳር በመሠረትኩ ጊዜ እኔ አልዳንኩ እንደ ነበር ታስቡ ይሆናል ለእናንተ እግዚአብሔር እንዲህ ይላችኃል ላገቡት ይህን ትእዛዝ እሰጣለሁ ይህም ትእዛዝ የጌታ እንጂ የእኔ አይደለም ሚሜስት ከባሏ አትለያይ ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር አለዚያ ከባሏ ጋር ትታረቅ ባልም ሚስቱን አይተዋት ወንድሞች ሆይ እያንዳንዱ ሰው በተጠራበት ሁኔታ ከእግዚአብሔርን ጋር ጸንቶ ይኑር ቆሮንቶስ ብ በመሰናከል ወጥመድ አማካይነት ከጽናታችሁ እንዳትናወጡ ይህ የጋብቻ ቃል ኪዳን ልባችሁ ውስጥ ዘልቆ ይግባ በነገር ሁሉ ፈቃዱን እንዲገልጥላችሁ እግዚአብሔር ለምነ ምናልባትም አንዳንዶቻችሁ አማኞች ብትሆኑም ትዳር የመሠረታችሁት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ላይሆን ይችላል ትዳራችሁን በተመለከተ ወደ እግዚአብሔር በረከት መግባት ከፈለጋችሁ ከማግባታችሁ በፊት የእርሱን ምክር ባለ መፈለጋችሁ ንስሐ አድርጉ እርሱም ይቅር ይላችኃል ሁለቴ መሳሳት አንድ ትክክለኛ ነገር እንደማያስገኝ ምን ጊዜም በልባችሁ ያዙ ከመሰናከል የተነሣ ቃል ኪዳን ማፍረስ የችግሩ መፍትሔ አይሆንም ጋብቻችሁን በተመለከተ ቃል እንዲሰጣችሁ ጌታን ፈልጉ ጽኑ መሠረት የተገለጠው የእግዚአብሔር ቃል ሕይወትና አገልግሎታችንን ልንመሠርትበት የሚገባ ጽኑ መሠረት ነው ለአጭር ጊዜ ብቻ ተሳታፊዎች ስለ ነበሩባቸው ቤተ ክርስቲያኖችና የአገልግሎት ተቋሞች ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሰዎች ነግረውኛል እነዚህ ሰዎች የሚንቀሳቀሱት ወይም ርምጃ የሚወስዱት በሚገጥሟቸው ችግሮች እንጂ በእግዚአብሔር ምሪት አለ መሆኑን ሳስብ ልቤ በጣም ያዝናል ችግሮቹ ምን ያህል ትልልቅ እንደ ነበሩ እነርሱና ሌሎች ወገኖች ላይ የደረሰው በደል እጅግ ከባድ እንደ ነበር እያጋነኑ ይናገራሉ በውሳኔያቸው ትክክል እንደ ነበሩ ያስባሉ ይሁን እንጂ የማያቀርቡት አጉል ምክንያት የራሳቸውን ደካማነት እንዳያዩ ግርዶሽ ይሆንባቸዋል ከአገልግሎት ተቋሞች ወይም ከቤተ ክርስቲያኖች ጋር አሁን ያላቸውን ግንኙነት ጊዜያዊ ይሉታል ወይም ደግሞ ለጊዜው እግዚአብሔር ያስቀመጠኝ ቦታ ይሉታል እንዲውም አንድ ጊዜ አንድ ሰው እዚህ ቤተ ክርስቲያን ያለሁት በውሰት ነው ሲል ሰምቻለሁ እንዲህ በማለት የሚናገሩት ነገሮች አስቸጋሪ ሲሆኑባቸው ወዲያውኑ ለመሸሽ ማምለጫ መንገድ እንዲሆንላቸው ነው በሚሄዱባቸው አዳዲስ ቦታዎች ሁሉ መሠረት የሚሆናቸው ነገር የለም ማዕበል በቀላሉ እየነዳ ቀጣዩ ወደብ ላይ ይጥላቸዋል ወደ ማን እንሄዳለን። ይል ነበር ግን እርሱ እንዲህ ነበር ያለው እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ ጸለይሁ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አበርታ ሉቃስ ኢየሱስ የጸለየው ጴጥሮስ ምንም ችግር እንዳይገጥመው አልነበረም እርሱ የጸለየው በዚያ ሂደት ውስጥ እምነቱ እንዳይጠፋ ነበር ከዚያ ከባድ መከራ በኃላ ስምዖን ጴጥሮስ ፍጻሜውን ለማሟላትና ወንድሞቹንም የሚያበረታበት አዲስ ባሕርይ እንደሚያዳብር ኢየሱስ ያውቅ ነበር የስምዖን ሴጴጥሮስን እምነት ለማጥፋት ክፉኛ ለማናወጥ ሰይጣን ፈቃድ ጠይቆ ነበር የጠላት ፍላጐት ያንን ታላቅ መገለጥ የተቀበለውን ያንን ታላቅ ዕምቅ ዐቅም የነበረውን ሰው ማጥፋት ነበር እግዚአብሔር ግን ለዚያ ነውጥ የተለየ ዓላማ ነበረው እንደ ሁልጊዜው ሁሉ እግዚአብሔር ሰይጣንን ቀድሞ ነበር ጠላት ይህን እንዲያደርግ የፈቀደው በስምዖን ጴጥሮስ ውስጥ ያለ ማንኛውም መናወጥ ያለበት ነገር እንዲናወጥ ነበር አንድን ነገር ማናወጥ አምስት ዓላማዎች አንዳሉት አንድ ወቅት ላይ ሚስቴ ሊዛ ተምራ ነበር የበለጠ ወደ መሠረቱ እንዲመጣ ለማድረግ የሞተውን ለማስወገድ የበሰለውን ለመሰብሰብ ለማንቃት ለመቀስቀስ ከእንግዲህ መለያየት እንዳይቻል አድርጐ ለማዋሐድ ወይም ለመቀላቀል መ ው ሠ ራስ ወዳድነት ወይም ትዕቢት ላይ የተመሠረተ ማንኛውም የአስተሳሰብ ሂደት ወይም የልብ ዝንባሌ መጥራት ተቆርጦ መጣል አለበት ከዚህ ከባድ ነውጥ የተነሣ የስምዖን ጴጥሮስ በራስ መተማመን ሁሉ ይወገዳል የሚቀረው ሁሉ በእግዚአብሔር ጽኑ መሠረት ላይ የተመሠረተው ብቻ ይሆናል ያለበትን ትክክለኛ ሁኔታ ለማወቅ ይነቃል የሞተው ይወገዳል የበሰለው ይሰበሰባል እርሱንም ወደ እውነተኛ መሠረት ያመጣዋል ከእንግዲህ በእግዚአብሔር ብቻ ይተማመናል እንጂ በራሱ መንገድና ሐሳብ አይንቀሳቀስም እርሱን እንደሚክድ በነገረው ጊዜ ጌታ ሆይ እኔ ከአንተ ጋር ወህኒ ለመውረድም ለመሞትም ዝግጁ ነኝ በማለት ጴጥሮስ በድፍረት ኢየሱስን ተከራክሮ ነበር ይህ ቃል በገዛ ራሱ ከነበረው እምነት እንጂ ከመንፈስ የመጣ አልነበረም ይህ ነውጥ የሚያስከትለውን ሁኔታ ገና ማየት አልቻለም ነበር ይሁዳና ስምዖን አንዳንድ ሰዎች ሴጥሮስ ብዙ የሚናገርና ፈሪ ነበር ይላሉ ሆኖም በአትክልቱ ቦታ የቤተ መቅደሱ ጥበቃ ጓዶች ኢየሱስን ለመያዝ በመጡ ጊዜ ጴጥሮስ ሰይፍ በመሰንዘር የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮ ቆርጦ ነበር ዮሐንስ መቼም ፈሪ ሰው በቁጥር በጣም የሚበልጡ የጠላት ወታደሮች ባሉበት እንዲህ አያደርግም እንደ እውነቱ ከሆነ ጴጥሮስ ብርቱ ሰው ነበር ብርታቱ ግን በራሱ ሰብዕና ነበር ምክንያቱም የመበጠሩ ሥራ ገና ስላልተጀመረ በትሕትና በእግዚአብሔር በመደገፍ የተገኘ ባሕርይ አልነበረም ልክ ኢየሱስ አስቀድሞ እንደ ተናገረው ነበር የሆነው ደፋሩ ብርቱውና ለኢየሱስ ለመሞት ዝግጁ መሆኑን የተናገረው ጴጥሮስ ብዙ ወታደሮች በነበሩበት አትክልት ቦታ ሰይፍ የመዘዘው ይኸው ስምዖን ሴጥሮስ በአንዲት ትንሽ የቤት ሠራተኛ ፊት ፈራ በጣም ከመደንገጡ የተነሣ ሌላው ቀርቶ ኢየሱስ የሚባል ሰው እንኳ እንደማያውቅ ካደ አንዳንዶች ሰዎችን የሚያሰናክሉ ትልልቅ ነገሮች ብቻ እንደ ሆኑ ያስባሉ ሆኖም ብዙ ጊዜ ሲያናውጡን የሚታዩት ትንንሽ ነገሮች ናቸው ይህም በራስ የመተማመንን ከንቱነት ያመለክታል ከዚያም ጴጥሮስ ለሁለት ተጨማሪ ጊዜ ኢየሱስን ካደ ወዲያውኑ ዶሮ ጮኸ ሌሴሌጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ አምርሮ አለቀሰ በራሱ የመተማመን ስሜቱ ሁሉ ተናወጠ ከእንግዲህ እንደ ገና መነሣት የሚችልም አልመሰለውም ምንም እንኳ እርሱ ባይገነዘበውም የቀሩለት ነገሮች ሁሉ በመንፈስ የተገለጡለት ነገሮች ብቻ ነበሩ ስምዖን ጴጥሮስና ይሁዳ በብዙ መንገድ ተመሳሳይ ናቸው በጣም መራራ በነበሩት የኢየሱስ መራራ ቀኖች እርሱን መካዳቸው ተመሳሳይ ያደርጋቸዋል ያም ሆኖ ግን ሁለቱ ሰዎች መሠረታዊ ልዩነትም ነበራቸው ስምዖን ኢየሱስን ባወቀበት ሁኔታ እርሱን ለማወቅ ይሁዳ ምንም ፍላጐት አልነበረውም ይሁዳ ኢየሱስ ላይ የተመሠረተ አልነበረም እርሱን ለመከተል ሁሉንም ትቶ መምጣቱ ከኢየሱስ ጋር አብሮ ወደ ተለያየ ቦታ መጓዙ ሌላው ቀርቶ ስደት በበረታበት ጊዜ ይሁዳ አብሮ መሆኑ ኢየሱስን የሚወድ አስመስሎት ነበር እርሱም እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት አጋንንት አስወጥቶአል ሕሙማንን ፈውሶአል ወንጌልንም ሰብኮአል እንዲሰብኩ እንዲፈውሱና አጋንንት እንዲያስወጡ ሁለት ሁለት እያደረገ ኢየሱስ የላከው ዐሥራ ሁለት ሐዋርያት እንጂ ዐሥራ አንድ እንዳልነበረ አስታውሱ ያም ሆኖ የከፈለው መሥዋዕት ኢየሱስን ከመውደዱ ወይም ስለ ማንነቱ ካገኘው መለኮታዊ መገለጥ የተነሣ አልነበረም ገና ከመጀመሪያውኑ ይሁዳ የራሱ አጀንዳ ነበረው ለራሱ ጥቅም ከማሳደድ ዝንባሌው ንስሐ አልገባም እንዲህ ባደርግ እናንተስ ምን ትሰጡኛላችሁ። በማለት ለሔዋን ጥያቄ ያቀረበ ጊዜ ያደረገው ይህንኑ ነበር ዘፍጥረት ዝጉ የእርሱን ባሕርይ ለማጠልሸትና ለማዛበት የእግዚአብሔርን ትእዛዝ አጣመመ እግዚአብሔር የተናገረው በአትክልት ስፍራው ውስጥ ከሚገኝ ከማንኛውም ዛፍ ፍሬ ትበላለህ ነገር ግን መልካምና ክፉን ከሚያሳውቀው ዛፍ አትብላ ምክንያቱም ከእርሱ በበላህ ቀን በእርግጥ ትሞታለህ በማለት ነበር ዘፍጥረት ያለ ጥርጥር እባቡ ለሔዋን እግዚአብሔር ከማንኛውም መልካም ነገር ከልክሏችኃል ማለቱ ነበር እንደ እውነቱ ከሆነ ግን እግዚአብሔር ከ በቀር ከማንኛውም ዛፍ ፍሬ በነጻነት ትበላለህ ነበር ያለው የአትክልት ቦታውን ሁሉና ከአንዱ በቀር በአትክልት ቦታው ያሉ ዛፎችን ፍሬ ሁሉ እንዲበላ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ሰጥቶ ነበር በእርግጥ እግዚአብሔር ለእናንተ አያስብም የሚያስብላችሁ ቢሆንማ ኖሮ እንዳትበሉ አይከለክላችሁም ነበር እናንተ እንደምታስቡት እርሱ አይወዳችሁም እንዲያውም እርሱ መልካም አምላክ አይደለም የሚል ትርጉም ያለው ሐሳብ በማቅረብ እባቡ ሴቲቱ ለእግዚአብሔር የነበራትን አመለካከት አጣመመ በመጨረሻም ተታለለች የእግዚአብሔርን ባሕርይ በተመለከተ ሐሰቱን አመነች ያኔ ኃጢአት የማድረግ ፍላጐቷ ተነሣሣ ምክንያቱም ከዚያ በኃላ የእግዚአብሔር ቃል ለእርሷ ሕይወት ሳይሆን ሕግ ሆኖባት ነበር የኃጢአት ኃይል ሕግ ነው ቆሮንቶስ ዛሬም ቢሆን ጠላት በዚህ መንገድ ይሠራል የአባታችን የእግዚአብሔርን ባሕርይ በተመለከተ ልጆቹ ጠማማ አመለካከት እንዲኖራቸው ያደርጋል ማንኛችንም አባቶችን አስተማሪዎችን የመሥሪያ ቤት አለቆችንና የመንግሥት ባለ ሥልጣኖችን የመሳሰሉ ራስ ወዳድና ክፉ ሰዎች አእናውቃለን እነዚህ ሰዎች ሥልጣንን የሚወክሉ በመሆናቸው እግዚአብሔርንም እነርሱን ባየንበት ዐይን እናየዋለን ምክንያቱም የመጨረሻው ባለ ሥልጣን አርሱ ነው ለምድራዊ አባቶቻችን ያለንን አመለካከት በማጣመም ጠላት በዘዴ ለአባታችን ለእግዚአብሔር ያለንን አመለካከትም አዛብቶአል ኢየሱስ ከመመለሱ በፊት የአባቶች ልብ ወደ ልጆች እንደሚመለስ እግዚአብሔር ይናገራል ሚልክያስ የእርሱ ባሕርይ ወይም ማንነት የእርሱ በሆኑ መሪዎች ይታያል ያ ደግሞ የፈውስ መተላለፊያ ይሆናል እግዚአብሔር እናንተን ለመጉዳት ምንም እንደማያደርግና በሕይወታችሁ የሚያደርገው ወይም የማያደርገው ማንኛውም ነገር ለእናንተ ዘላቂ ጥቅም እንደ ሆነ ካወቃችሁ በነጻነት ራሳችሁን ትሰጡታላችሁ ለጌታ ሞትን እንኳ ለመቀበል ዝግጁ ትሆናላችሁ ሙሉ በሙሉ ራሳችሁን ለኢየሱስ ከሰጣችሁና በእርሱ ጥበቃ ከተማመናችሁ በፍጹም አትሰናከሉም ምክንያቱም ከእንግዲህ እናንተ የራሳችሁ አይደላችሁም የሚጐዱትና ተስፋ የሚቆርጡት በማንነቱ በመታመን ሳይሆን አንዳች ነገር ጠብቀው ወይም ፈልገው ወደ እርሱ የመጡት ናቸው የዚያ ዐይነት ዝንባሌ ካለን በቀላሉ ተስፋ እንቆርጣለን ራስን ማዕከል ያደረገ ሕይወት በቅርብ ያለውን ብቻ እንድናይ ያደርገናል አሁን ያለንበትን ሁኔታ በእምነት ዐይን አናይም ሕይወታችን በእውነት በክርስቶስ የተዋጠ ከሆነ ባሕርዩን እናውቃለን የደስታው ተካፋዮችም እንሆናለን ከእንግዲህ ጨርሶ አንናወጥም ወይም ተስፋ አንቆርጥም ነገሮችን የምንመዝነው አካባቢውን ወይም ሁኔታውን በማየት ከሆነ በቀላሉ እንሰናከላለን በመንፈስ ዐይን ማየት ግን እንዲህ አይደለም ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር መልስ የሚሰጠኝ እኔ በጣም አስፈላጊ ነው ባልኩት ጊዜ ሁኔታና መጠን አይደለም ሆኖም ወደ ኃላ ዘወር ብዬ እያንዳንዱን ነገር ስመለከት የእርሱን ጥበብ አያለሁ ብዙ ጊዜ ልጆቻችን እነርሱን የምናስተምርበትን ዘዴ ወይም ከዚያ ጀርባ ያለውን ዓላማ ምክንያት አይረዱልንም ከዚያ እንዲጠቀሙ በማሰብ ለታላላቆቹ ልጆች ገለጻ መስጠት እንሞክራለን አልፎ አልፎ ግን እነርሱም ቢሆኑ ካለመብሰላቸው የተነሣ ላይረዱ ወይም ላይስማሙ ይችላሉ የኃላ ኃላ ግን መረዳታቸው አይቀርም አንዳንዴ ዓላማው ታዛዥነታቸውን ፍቅራቸውንና ብስለታቸውን ለመፈተን ሊሆን ይችላል በሰማይ ያለው አባታችንም እንደዚህ ያደርጋል እንዲህ ባሉ ሁኔታዎች ውስጥ እምነት መምንም እንኳ መረዳት ባልችልም እተማመንብሃለሁ ይላል ዕብራውያን ላይ እግዚአብሔር የሰጣቸው የተስፋ ቃል ሲፈጸም ባያዩ እንኳ ሳይናወጡ ጸንተው ስለ ቆሙ ሰዎች ሲናገር ሌሎቹ ደግሞ የተሻለውን ትንሣኤ ለማግኘት ሲሌ መትረፍን ንቀው ለሞት ለሚዳርግ ሥቃይ ራሳቸውን ሰጡ ከዚያም ነጻ ለመውጣት አልፈለጉም አንዳንዶቹ መዘባበቻ ሆኑ ተገረፉ ሌሎቹ ደግሞ ታስረው ወደ ወህኒ ተጣሉ በድንጋይ ተወገሩ በመጋዝ ለሁለት ተሰነጠቁ እየተጐሳቆሉ እየተሰደዱና እየተንገላቱ የበግና የፍየል ቆዳ ለብሰው ዞሩ ዓለም ለእነርሱ አልተገባቻቸውምና በየበረሐውና በየተራራው በየዋሻውና በየጉድጓዱ ተንከራተቱ እነዚህ ሁሌ ስለ እምነታቸው የተመሰከረላቸው ቢሆኑም ከእነርሱም ማንም የተስፋውን ቃል የተቀበለ የለም የሚለውን ጽሑፍ እናያለን የሚከፈለው ዋጋ ምንም ይሁን ምን እነርሱ የፈለጉት ራሱ እግዚአብሔርን ነበር የተገባላቸው ተስፋ ቃል ሲፈጸም ባያዩ እንኳ አምነውበታል እንዲህ ያሉ ሰዎች አይሰናከሉም። በማለት ጸለየ እርሱን ለማገልገል ለተዋቸው ነገሮች ሁሉ እግዚአብሔርን እንደ ባለ ዕዳ ቆጠረ ብዙ ሰዎች ከዚህ ያነሰ አንዳንዴም ከዚህ የከፋ ጉዳትና ተስፋ መቁረጥ ደርሶባቸዋል ብዙዎችም በራሱ በጌታ ላይ ተሰናክለዋል ለእርሱ አደረግን የሚሉትን ሁሉ ግምት ውስጥ የማስገባት ግዴታ ያለበት ይመስላቸዋል እነዚህ ሰዎች ሲያገለግሉ የነበረው በተሳሳተ ምክንያት ነበር እግዚአብሔርን ማገልገል ያለብን ስለ ማንነቱና አስቀድሞ ስላደረገልን እንጂ ገና ወደ ፊት ያደርግልናል ብለን ስለምንጠብቀው ነገር መሆን የለበትም በእርሱ የተሰናከሉ ወገኖች እነርሱ ነጻ እንዲሆኑ ምን ያህል ከባድ ዕዳ እንደ ተከፈለላቸው ገና በሚገባ አልተረዱም ከእንዴት ዐይነት ሞትና ጥፋት እንደ ታደጋቸው ዘንግተዋል እነዚህ ሰዎች የሚያዩት በጊዜያዊው እንጂ በዘላለማዊው ዐይን አይደለም ያ ወጣት ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ አቆመ ከአጓጉል ጓደኞች ጋር ቡና ቤቶችና ፓርቲዎች ማዘውተር ጀመረ በጣም ተስፋ ቆርጦና ተናድዶ ስለ ነበር ከእግዚአብሔር ነገር ጋር ምንም ግንኙነት እንዲኖረው አልፈለገም ሆኖም በዚህ ዐይነት አኗኗር ከሁለት ሳምንት በላይ መቀጠል አልቻለም ልቡ በጣም ተወቅሶ ነበር በዚያ ሁኔታ ውስጥ እንኳ ሆኖ ለስድስት ወር ያህል ወደ ጌታ መቅረብ አልፈለገም ነበር ያኔም ቢሆን ሰማይ የነሐስ ያህል ሆኖበት ነበር የእግዚአብሔር መገኘት በጣም ርቆት ነበር ከአንድ ዓመት በላይ አለፈ በተለያዩ አጋጣሚዎች እግዚአብሔር አሁንም በሕይወቱ ሥራ ላይ መሆኑን ማየት ቻለ እርሱም ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ጀመረ በዚህ ጊዜ ሁኔታው ከበፊቱ በጣም የተለየ ነበር አሁን ትሑት ሆኖአል የፈተናው ጊዜ ካለፈ በኃላ በፍጹም እርሱን እንዳልጣለው እግዚአብሔር አሳየው መንፈሳዊ ሕይወቱ እየታደሰ ሲመጣ በራሱ ብርታት ሳይሆን ትምክህቱን በእግዚአብሔር ጸጋ ላይ ማድረግን ተማረ እኔም በየጊዜው አገኘው ነበር ከአንድ ዓመት ተኩል በኃላ ይኖራሉ ብሎ ያላሰባቸው ነገሮች በሕይወቱ መኖራቸውን ማየት እንደ ቻለ አጫወተኝ መልካም ምግባር የጐደለኝና ከሰዎችም ጋር ጥሩ ግንኙነት ያልነበረኝ ነበርኩ በሰዎች ዓይን ብርቱ ሆፔ መታየት እንዳለብኝ እየነገረ ነበር አባቴ ያሳደገኝ ይህ አስተዳደጌ እግዚአብሔር የሚፈልገው ዐይነት አልነበረም በዚያ ሁኔታ ውስጥ ስላልተወኝ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ ልቤን በጣም ያሳዘነው በየቡና ቤቱ መዞሬና መጠጣቴ አልነበረም በጣም ያሳዘነኝ ለመንፈስ ቅዱስ ጀርባዬን ማዞሬ ነበር አሁን በጣም ነው የምወደው ከእርሱ ጋር የነበረኝ ኅብረት የአሁኑን ያህል ጣፋጭ ሆኖ አያውቅም በሕይወቱ ብዙ ነውጥ ደረሰ በዚያ ውስጥ በራሱ የመተማመን ዝንባሌው ጥሎት ጠፋ አሁን ያ ወጣት ስምዖን ጴጥሮስ የነበረው ዐይነት መሠረት አለው ያ በፍጽም አይወሰድበትም ሕይወትና አገልግሎቱን ትዕቢት ላይ ሳይሆን የእግዚአብሔር ጸጋ ላይ መሥርቶአል መሰናክል በሕይወታችን ያለውን ድካምና የምንሰበርበትን ነጥብ ግልጽ ያደርጋል ብዙ ጊዜ ብርቱዎች እንደ ሆንን ያሰብነው ደካማነታችን የተሸፈነበት ቦታ ነው ከባድ ዐውሎ ነፋስ መጥቶ እስኪገልጠው ድረስ እንደ ተደበቀ ይቀራል ሐዋርያው ጳውሎስ እኛ በእውነት የተገረዝን በእግዚአብሔር መንፈስ የምናመልክ በክርስቶስ ኢየሱስ የምንመካ በሥጋም የማንታመን ነንና በማለት ይጽፋል ፊልጵስዩስ በራሳችን ችሎታ ዘላላማዊ ዋጋ ያለው ነገር ማድረግ አንችልም እንዲህ ማለት ቀላል ነው ይህ እውነት በጥልቅ እኛነታችን ውስጥ ሥር መሰደዱ ግን የተለየ ነገር ነው ሰዎች እንዳይሰናከሉ በማለት ኢየሱስ እውነትን አልሸፋፈነም ይኒኔዕማ ሃየተሰኘው መጽሐፍህ ዐይኖቼን ገልጦልኛል እኔና ባሌ አገልግሎት ውስጥ ነው ያለነው ከጌታ ጋር ያለኝ ግንኙነት በሙሉ ትከከል እንደ ሆነ አስብ ነበር ለዐሥራ አምስት ዓመት ያህል አክስቴ ላይ ይፔው የነበረ ቂም ማንኛውንም ዋጋ ሊያስከፍለኝ ነበር እንደ ከርስቲያኖች ይቅር ማለት እንዳለብን ብዙ ጊዜ እንማራለን ይሁን አንጂ መልእከትህ ያለፈ ዘመን ጉዳቴን ፊት ለፊት እንድጋፈጥ አስካደረገኝ ጊዜ ድረስ ይህን ያህል ወደ ልቤ አልገባም ነበር አር ኤም ቴኔሲ የመሰናከያ ዐለት ፖ ዶፆሥመረጠና ታረ ዖማጳ ድሯቋጋይ ዕጽሥ ዳኖራሥ ኋረታ ዖ። ዴዎሮዕ ፁፅ ዚህ ዘመን ማመን የሚለው ቃል ትክክለኛ ትርጐሙን እያጣ በ ብዙዎች የሚገምቱት አንድን እውነት ወይም ሐቅ መቀበል መሆኑን ነው ለብዙዎች ከመታዘዝ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ከላይ ባለው ምንባብ ግን ማመንና አለመታዘዝ ተቃራኒ መሆናቸው ነበር የቀረበው መጽሐፍ ቅዱስ በእርሱ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ሁሉ የዘላላም ሕይወት አለው እንጂ አይጠፋም ይላል ዮሐንስ ማመን ለሚለው ቃል ካለን የተሳሳተ አስተሳሰብ የተነሣ ሰዎች ማድረግ ያለባቸው ኢየሱስ የሚባል ሰው በዚህ ምድር እንደ ነበርና በኃላም መስቀል ላይ ተሰቅሎ እንደ ሞተ ማመን ብቻ እንደ ሆነ ያስባሉ ይህን ካደረጉም ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት እንደሚስተካከል ያስባሌ የሚያስፈልገው ይኸው ብቻ ቢሆን ኖሮ አጋንንትም ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ግንኙነት ይስተካከል ነበር መጽሐፍ ቅዱስ አንድ እግዚአብሔር እንዳለ ታምናለህ መልካም ነው አጋንንትም ይህንኑ ያምናሉ በፍርሀትም ይንቀጠቀጣሉ ይላል ያዕቆብ ያም ሆኖ ግን ድነት ለእነርሱ አልተሰጠም በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት ማመን የተሰኘው ቃል የአንድን ነገር መኖር ከመቀበል ወይም አንድ ነገር እውነት መሆኑን በአእምሮ ከመስማማት የበለጠ ትርገኣኤም አለው እንግዲህ ከላይ ያለውን ጥቅስ በዐውዱ መሠረት ስንመለከተው የማመን ዋናው ጉዳይ መታዘዝ መሆኑን ነው የምንረዳው ስለዚህም እንግዲህ ለእናንተ ለምታምኑት እርሱ ክቡር ነው ለማይታዘዙት ግን ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ ደግሞም ሰዎችን የሚያሰናክል የሚጥላቸውም ዐለት ሆነ በሚል መልኩ ማንበብ እንችላለን ራሳችሁን የሰጣችሁትን አምላክ ባሕርይና ፍቅር በሚገባ ካወቃችሁ ለእርሱ መታዘዝ አይከብዳችሁም ከጌታ ጋር የሚኖረን መቀራረብ መሠረቱ ፍቅር ነው እዚህ ላይ ፍቅር ስንል የእርሱን መርሖዎች ወይም ትምህርቶች መወደድ ማለት ሳይሆን ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስን መውደድ ማለት ነው ፍቅር በጽናት ቦታውን ካልያዘ ለመሰናከልና ተፍገምግሞ ለመውደቅ የተጋለጥን እንሆናለን እግዚአብሔር ግንበኞች በማለት የጠራቸው እስራኤላውያን የእግዚአብሔር የማእዘን ድንጋይ የሆነውን ንቀውት ነበር የብሉይ ኪዳን ትምህርታቸውን ወድደዋል የራሳቸውን ጥቅም ማስጠበቂያና ሌሎችን መቆጣጠሪያ አድርገው ሊጠቀሙበት ስለሚችሉም በቅዱሳት መጻሕፍት አተረጓጐማቸው ረክተዋል በሌላ በኩል ደግሞ እነርሱ አጥብቀው የያዙትንና በጣም የሚወዱትን ወገኝነት ሁሉ ኢየሱስ ሞግቶባቸው ነበር በእነርሱ የዘላለም ሕይወትን የምታገኙ እየመሰላችሁ መጻሕፍትን ትመረምራላችሁ እነዚሁ መጻሕፍት ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው በማለትም ዕቅጩን ነግሮአቸው ነበር ዮሐንስ ገና ከጅማሬው አንሥቶ እግዚአብሔር ይፈልግ የነበረው ከእርሱ ጋር ኅብረት የሚያደርጉ ወንዶችና ሴቶችን እንደ ነበር መቀበል ጨርሶ ሊዋጥላቸው አልቻለም ይልቁንም እነርሱ ገፐችና የበላይ መሆንን ነበር የፈለጉት ከእግዚአብሔር ጋር ሊኖር ይገባው ከነበረ ቀረቤታ የበለጠ በእነርሱ ዐይን ሕጉ ከፍ ያለውን ቦታ ይዞ ነበር በነጻ የተሰጣቸውን ንቀዋል እነርሱ የሚፈልጉት ዋጋ የከፈሉበትንና በልፋታቸው ማግኘት የሚችሉትን ነበር ስለሆነም የእግዚአብሔር ነጻ ስጦታ የሆነው የሕይወታቸውና የድነታቸው ተስፋ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያሰናክልና የሚጥል ዐለት ሆነባቸው በቤተ መቅደስ ውስጥ ስምዖን ሕፃኑ ኢየሱስን በክንዶቹ ይዞ በነበረ ጊዜ ይህ ሕፃን በእስራኤል ለብዙዎች መነሣትና መውደቅ ምክንያት ይሆናል የሚል ትንቢት ተናግሮ ነበር ሉቃስ መውደቅና መነሣት የሚሉትን ቃሎች ልብ አድርጉ ለዓለም ሰላም እንዲያመጣ የመጣው ኢየሱስ የእርሱ ለነበሩ ወገኖች መለያየትን የሚያመጣ ሰይፍ ሆነ ማቴዎስ በግንበኞቹ በዚያ ዘመን የሃይማኖት መሪዎች የነበሩት ሲጠቁ ለነበሩትም ሕይወት ሆነላቸው ኢየሱስና መሰናከያዎች እሑድ ትምህርት ቤት ውስጥ ብዙ ጊዜ ስለ ኢየሱስ የሚቀርብልን ምስል እረኛው አንድ ጠፍቶ የነበረ በግ በትከሻው ተሸክሞ ወደ በረቱ ሲመልሰው የሚያመለክት ነው ወይም ደግሞ ሕፃናትን ለመባረክ እጆቹን በእነርሱ ዙሪያ በማድረግ ፈገግ ብሎ እወዳችኃለሁ የሚል ሰው ምስል ነው እነዚህ ሁሉ እውነት ናቸው ይሁን እንጂ ሙሉውን ስዕል አይሰጡንም ይኸው ኢየሱስ ራሱ እናንተ እባቦች የእፉኝት ልጆች። አሉት ማቴዎስ የሰጣቸውን መልስ ልብ አድርጋችሁ አንብቡ የሰማዩ አባቴ ያልተከለው ተክል ሁሉ ይነቀላል ተዉአቸው እነርሱ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውር መሪዎች ናቸው ዕውር ዕውርን ቢመራ ሁለቱም ተያይዘው ገደል ይገባሉ ማቴዎስ መሰናከል በእውነት በእግዚአብሔር ያልተተከሉ ሰዎችን እንደሚያስወግድ ኢየሱስ ያመለክታል አንዳንድ ሰዎች የቤተ ክርስቲያን አባሎች የአገልግሎት ቡድን ተባባሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ ያ ማለት ግን የግድ ከእግዚአብሔር ወገን ናቸው ማለት አይደለም እውነት ሲሰበክ ሊኖር የሚችለው መሰናክል እውነተኛ ዓላማቸውን ይገልጣል እነርሱም ይነቀላሉ በአገልግሎት በተዘዋወርኩባቸው ቤተ ክርስቲያኖች ከቤተ ክርስቲያን ሥራ ወይም ከማኅበረ ምዕመናኑ ተለይተው በሄዱ ሰዎች ፓስተሮች እያዘኑ ሲናገሩ ሰምቻለሁ አብዛኛውን ጊዜ እነዚህ ሰዎች ደስ ያልተሰኙት እውነት በመሰበኩና የአኗኗር መንገዳቸውን ፊት ለፊት የሚጋፈጥ ሆኖ በመገኘቱ ነው ከዚያ በኋላ ማንኛውንም የቤተ ክርስቲያን ገጽታ መንቀፍና መተቸት ይጀምራሉ በመጨረሻም ትተው ይሄዳሌ አንዳንድ ፓስተሮች ወደ ቤተ ክርስቲያናቸው የሚመጣ ሁሉ ተመልሶ እንዳይሄድ አጥብቀው ስለሚፈልጉ እውነትን ያመቻምዎቻሉሌ እንዲህ ያሉ ፓስተሮችን እውነትን ከተናገራችሁ ሰዎችን ታስቆጡ ይሆናል ምናልባትም ትተው ይሄዱ ይነቀሌ ይሆናል ይህን በማድረጋቸው በፍጹም አትዘኑባቸው ይልቁንም እግዚአብሔር ወደ እናንተ ለሚያመጣቸው ሰዎች እውነትን መናገራችሁን ቀጥሉ እላቸዋለሁ አንዳንድ መሪዎች ሰዎችን እንዳያጡ ስለሚፈሩ ፊት ለፊት መጋፈጥ አይፈልጉም በተለይ ደግሞ ፊት ለፊት መጋፈጥ የሚገባቸው ሰዎች ጠቀም ያለ ገንዘብ የሚሰጡ ወይም በማኅበረ ሰቡም ሆነ በቤተ ክርስቲያን ተሰሚነት ያላቸው ከሆነ የበለጠ ወደ ኃላ ይላሉ ሌሎች ደግሞ ለረጅም ጊዜ ከእነርሱ ጋር የኖሩ ሰዎችን ስሜት እንዳይጐዱ ይፈራሌ ከዚህም የተነሣ ፓስተሮቹ እግዚአብሔር በአደራ የሰጣቸውን መንጋ የመጠበቅና የመመገብ ሥልጣናቸውን ያጣሉ ፓስተር በሆንኩባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ላይ አንድ አስተዋይ ሰው ሥልጣንህን ጠብቅ አለበለዚያ ሌላው ከአንተ ወስዶ አንተ ላይ ይጠቀምበታል በማለት አስጠንቅቆኝ ነበር ሳሙኤል ለማንም ሰው እውነትን ከመናገር ወደ ኃላ የማይል ሰው ነበር ሌላው ቀርቶ ለንጉሥ እንኳ እውነትን ለመናገር አልፈራም ሳኦል ሳይታዘዝ በቀረ ጊዜ ፊት ለፊት እንዲጋፈጠው እግዚአብሔር ለሳሙኤል ነግሮት ነበር እርሱም እንደ ተነገረው አደረገ በጣም የሚያሳዝነው ግን ሳኦል ለእግዚአብሔር ቃል የሰጠው ምላሽ እውነተኛ ንስሐ በማድረግ አልነበረም ሳሙኤል ተለይቶት ለመሄድ ሲነሣ ሳኦል ልብሱን ጨምድዶ ይዞ ስለ ነበር የሳሙኤል ልብስ ጫፍ ተቀደደ ከዚያም እግዚአብሔር የእስራኤልን መንግሥት ዛሬ ከአንተ ቀድዶታል በማለት አስደነገጠው ሳሙኤል ሳሙኤል ለሳኦል የፈለገው ይህን አልነበረም በሆነው ነገር በጣም አዝኖለታል ሳኦልን ለንጉሥነት ቀብቶት ነበር ስለ መልካም አመራር ሥልጠና ሰጥቶት ነበር የንግሥና ሥርዐቱን የፈጸመውም እርሱ ነበር ሳሙኤል የሳኦል የቅርብ ወዳጅ ነበር ሆኖም ሳሙኤል ለሳኦል በማዘኑ እግዚአብሔር የሰጠውን ምላሽ ስሙ በእስራኤል ላይ እንዳይነግሥ ለናቅሁት ለሳኦል የምታለቅስለት እስከ መቼ ነው። አላቸው በዙሪያው ወደ ተቀመጡትም በመመልከት እንዲህ አለ እናቴና ወንድሞቼ እነዚህ ናቸው የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ወንድሜ እኅቴ እናቴም ነውና ማርቆስ የገዛ ቤተ ሰቡ ሰዎች አእምሮውን ስቶአል በማለት ነበር ያሰቡት ዘመዶቹ ወደ ነበረበት ቦታ የመጡት ይዘው ሊወስዱት እንደ ነበር መናገሩን ልብ አድርጉ እነዚህ ሰዎች እነማን እንደ ነበሩ ማርቆስ ሲያመለክት እናቱና ወንድሞቹ ነበሩ ይላል በኃላም አንድ ሰው ቤት ውስጥ ሲሰብክ አግኝተውት ነበር የዮሐንስ ወንጌል የገገ ወንድሞቹ እንኳ አላመኑበትም ነበር ይላል ዮሐንስ ኢየሱስ በጣም ይቀርቡት በነበሩ ሰዎች መናቁን ብዙዎች አልተረዱም ይሁን እንጂ እርሱ ይፈልግ የነበረው የቤተ ሰቡን ወይም በጣም ይቀርቡት የነበሩ ሰዎችን ይሁንታ አልነበረም ሰዎች መስማት በሚፈልጉት መሠረት አልነበረም ይንቀሳቀስ የነበረው እነርሱ ቢወዱትም ቢጠሉትም የአባቱን ዕቅድ መፈጸም ነበር ዓላማው ኢየሱስን ከተከተልን ጓደኛችን ወይም ቤተ ሰባችን ይሰናከሉብናል በማለት የሚያስቡ ብዙ ሰዎችን በተለይም ባለ ትዳር ወገኖችን አይቻለሁ ከዚህም የተነሣ ከእምነት ወደ ኃላ ብለዋል ወይም በጥሪያቸው መሠረት መኖር አልፈለጉም እኔ ዳግም የተወለድኩ ጊዜ ቤተ ሰቦቼ በሙሉ ካቶሊኮች ነበሩ አዲስ በተቀበልኩት እምነት የነበረኝን ደስታ አልተጋሩኝም ነበር በተለይም እናቴ እኔን ያሳደገችበትን ቤተ ክርስቲያን ትቼ በመሄዴ በጣም ከፍቷት ነበር እግዚአብሔርን በጣም የሚወዱ ካቶሊኮች እንዳሉ እርግጠኛ ነኝ እኔን በተመለከተ ግን ከዚያ ቤተ ክርስቲያን መውጣት እንደ ነበረብኝ አውቃለሁ ሁለተኛው አስደንጋጭ ነገር የተሰማው ወደ አገልግሎት ለመግባት የወሰንኩ ጊዜ ነበር ከኾርዱ ዩኒቨርስቲ በሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ዲግሪዬን ያገኘሁት በቅርቡ ነበር ወላጆቼ በእኔ ላይ ከፍተኛ ተስፋ ጥለው ነበር በበኩሌ ግን ለእኔ እግዚአብሔር የሚፈልገውን አውቅ ነበር ያንን ማድረጌ የቅርቤ የሆኑትን እንደሚያሰናክልም አውቅ ነበር ይህም ለዓመታት ዘልቆ ነበር በመካከላችን ብዙ አለመግባባት ነበር ይሁን እንጂ የቱንም ያህል ሊቆጡ ቢችሉም ኢየሱስን መከተል ነበረብኝ መጀመሪያ ላይ በወንጌል ፀጥ ላሰኛቸው ሞክሬ ነበር በማስቀደሳቸው ወይም ቅዱስ ቁርባን በመቀበላቸው ብቻ ድነት እንደማያገኙ ነግሬአቸው ነበር በየጊዜው እየተከራከርኩ ወደ ትዕግሥታቸው ጫፍ አድርሻቸው ነበር አሁን ላይ ሆፔ ሳስበው ያደረግሁት ትክክል እንዳልነበረ ተረድቻለሁ በኃላ ግን በእነርሱ ፊት እውነተኛ ክርስትና ሕይወት መኖር እንዳለብኝና መልካም ሥራዬን እንዲያዩ ማድረግ እንዳለብኝ እግዚአብሔር አመለከተኝ ያም ሆኖ አሁንም ቢሆን እነርሱን ደስ ለማሰኘት ስል እውነትን ማመቻመች አልፈልግም አሁን ወላጆቼ በአገልግሎቴ በጣም እየደገፉኝ ነው በጣም ይከራከረኝ የነበረው ወንድ አያቴ በሰማንያ ዘጠኝ ዓመቱ ማለትም ከመሞቱ ሁለት ዓመት ቀደም ሲል በአስደናቂ ሁኔታ ድነት አግኝቷል የኢየሱስ እናትና ወንድሞች አእምሮውን ስቶአል በማለት አስበው ነበርጉ ሆኖም ለእግዚአብሔር በመታዘዙ በበዓለ ሃምሳ ቀን በሰገነቱ በነበሩ ጊዜ ሁሉም ድነዋል በአንድ በኩል ወንድሙ የነበረው ያዕቆብ በኢየሩሳሌም የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ዋና ሐዋርያ ሆኗል የቤተ ሰባችንን ሰዎች ደስ ለማሰኘት በማሰብ እግዚአብሔር የነገረንን ከማድረግ ወደ ኃላ የምንል ከሆነ በሕይወታችን ሊኖር የሚገባውን ትኩስ ዘይት እናጣለን እነርሱም ነጻ እንዳይሆኑ እናግዳቸዋለን ሏፈይቶዕ ዳዝሇረውት ዲያሃሰቋሃ ያነያሩም ዳሪና«ሯፈልጳ ባለፈው ምዕራፍ ኢየሱስ ባሰናከላቸው ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ይዘው ስለ ነበረው ዐቋም በሰፊው ተመልክተን ነበር እስቲ እንደ ገና እንይ ጉዳዩን ከኢየሱስ አንጻር ለመመልከት እንሞክር ደቀ መዛሙርቱ በዚህ ነገር ማጉረምረማቸውን ኢየሱስ በገዛ ራሱ ተረድቶ እንዲህ አላቸው ይህ ዕንቅፋት መሰናከያ ይሆንባችኃልን። መሰናክል መምጣቱ አይቀርምና ነገር ግን የመሰናከሉ ምክንያት ለሚሆን ሰው ወዮለት እጅህ ወይም እግርህ ለመሰናክል ምክንያት ቢሆንብህ ቆርጠህ ጣለው ሁለት እጅ ወይም ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ዘላለም እሳት ከምትጣል አንካሳ ወይም ሸባ ሆነህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል እንዲሁም ዐይንህ ለመሰናክል ምክንያት ቢሆንብህ አውጥተህ ጣለው ሁለት ዐይን ኖሮህ ወደ ገሃነም እሳት ከምትጣል አንድ ዐይን ኖሮህ ወደ ሕይወት መግባት ይቫልሃል ከእነዚህ ከታናናሾች መካከል አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ እላችኃለሁና በሰማይ ያሉት መላእክቶቻቸው በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ሁልጊዜ ያያሉ ማቴዎስ ይህ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ሙሉ በሙሉ የሚናገረው ስለ መሰናክል ነው ሌላው ቀርቶ አዲስ ኪዳን የሰጠን መብት ቢሆን እንኳ በምንም መልኩ የኃጢአት ምክንያት መሆን እንደሌለብን ኢየሱስ በጣም ግልጽ አድርጐአል ወንድማችሁን የሚያሰናክል ወይም ኃጢአት እንዲያደርግ ምክንያት የሆነ ማንኛውንም ነገራችሁን ቆርጣችሁ ጣሉት ምናልባት ቀደም ሲል ከነበረው ምዕራፍ ከተመለከትነው በመነሣት እንዲህ ከሆነ ኢየሱስ ብዙ ሰዎችን ለምን አሰናከለ በማለት ግራ እንጋባ ይሆናል መልሱ በጣም ቀላል ነው ኢየሱስ አንዳንድ ሰዎችን ያሰናከለው ለአባት ከመታዘዙና ሌሎችን ከማገልገሉ የተነሣ ነበር እርሱ ሌሎችን ያሰናከለው የገዛ ራሱን መብት ለማስከበር ሲል አልነበረም በሰንበት ዕለት በመፈወሱ ፈሪሳውያን ተሰናክለው ማለትም ተቀይመው ነበር ደቀ መዛሙርቱ የተሰናከሉት አባቱ የሰጠውን እውነት በመናገሩ ነበር ማርያምና ማርታ የተሰናከሉት አልዓዛርን ለመፈወስ ቶሎ ባለ መምጣቱ ነበር ይሁን እንጂ ራሱን ለማገልገል ወይም ለመጥቀም ሲል ኢየሱስ ማንንም ሲያሰናክል አናይም ለቆሮንቶስ ሰዎች በጻፈው መልእክት ጳውሎስ ይህን ማስጠንቀቂያ ይሰጣል ነገር ግን ከነጻነታችሁ የተነሣ የምታደርጉት ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆን ተጠንቀቁ ቆሮንቶስ ነጻነታችን የተሰጠን ሌሎችን እንድናገለግልና ሕይወታችንንም እንድንሰጥ ነው መገንባት እንጂ ማፍረስ የለብንም ይህ ነጻነት የተሰጠን ነገሮችን እንድናጠራቅም አይደለም ይሁን እንጂ በዚህ መንገድ ስለ ተጠቀምንበት በክርስቲያኖች አኗኗር ብዙዎች ተሰናክለዋል ቆሮንቶስ ላይ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ እንደ ገና ስሙ ነገር ግን ከነጻነታችሁ የተነሣ የምታደርጉት ለደካሞች ፅንቅፋት እንዳይሆን ተጠንቀቁ ይህን ትእዛዝ በእንዴት ዓይነት ሁኔታ ልናፈርስ እንደምንችል አንድ ምሳሌ ይኸውላችሁ ለሁለተኛ አገልግሎት ወደ ኢንዶኔዥያ በሄድኩ ጊዜ ሚስቴ ሊዛን ልጆቼንና ሞግዚታቸውን ይፔ ነበር የሄድከት የመዝናኛ ደሴት ወደ ሆነችው ዴንፓሳር ባሊ መጣን እኛ የምናገለግልበት ቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ የነበረ ሰው በጣም ጩኸት በበዛበት የከተማው ክልል ውስጥ አንድ መጠነኛ ሆቴል ነበረው ረጅም ርቀት ነበር የተጓዝነው በዚህ ላይ ደግሞ በቂ እንቅልፍ አላገኘንም ነበር በጣም ደካክሞን ነበር እዚያ ባሳለፍነው ሌሊት በሰዎች ጫጫታና በውሾች ጩኸት ብዙ ጊዜ እንባንን ነበር እዚያ ያሳለፍነው አንድ ሌሊት ቢሆንም የምንፈልገውን እንቅልፍ አላገኘንም ነበር በሚቀጥለው ቀን ወደ ጃቫ ሄደን በጣም በተጨናነቀ ፕሮግራም ውስጥ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንቶች አገለገልን በእነዚያ ሁለት ሳምንቶች ውስጥ የነበረን ነጻ ቀን አንድ ብቻ ነበር ያም ቢሆን ለጉዞ የምናውለው ነበር በቀኑ ውስጥ ባሉት ሃያ አራት ሰዓቶች ውስጥ ሰላሣ ሺህ አባሎች በነበሩት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቀን አምስት ጊዜ አገልግለን ነበር ጉዞአችን መጨረሻ ላይ በባሊ በኩል እንድንመለስ ነበር ያሰብነው እንደ ገና በቤተ ክርስቲያን ሽማግሌው ሆቴል እንድናርፍ ፓስተሩ ነገረን ሁለት ሳምንት ሙሉ ያለ በቂ ዕረፍት በአገልግሎት ካሳለፍን በኃላ በድጋሚ እዚያ ቦታ ማረፍ ደስ አላለንም ጃቫን ለቅቀን በምንሄድበት ቀን ጠዋት ቁርስ ላይ እያለን ባሊ ውስጥ ካሉት በጣም ምርጥ ሆቴሎች በአንዱ እንድናርፍ አንዲት ደግ ሴት ሙሉ ወጪያችንን እንደምትሸፍንልን ነገረችን የምንፈልገውን ዕረፍት ማግኘት የምንችልበትና በዚያ ውብ ቦታ ጊዜ ማሳለፍ ስለምንችል በጣም ነበር ደስ ያለኝ ከነበርንበት ሬስቶራንት ለመነሣት ዕቃዎቻችንን እያዘገጃጀን እያለ ሴትዮዋ ባቀረበችው ሐሳብ ደስ አለመሰኘትዋን ሊዛ ነገረችኝ እኔና አስተርጓሚው ግን ብትከፍልልን ጥሩ ሊሆን እንደሚችል ልናሳምናት ሞከርን ከጃቫ ወደ ባሊ ለመሄድ አውሮፕላን ውስጥ እያለን ሊዛ ትክክለኛ ነገር እያደረግን እንዳይደለ በድጋሜ ነገረችኝ የነገረችኝን ባለ መስማቴ ሞኝነቴ የታወቀኝ በኃላ ነበር ቤተ ክርስቲያኑን ምንም ገንዘብ የማያስወጣ በመሆኑ እያደረግን ያለው ጥሩ እንደ ሆነ ነገርኳት ባሊ ስንደርስ ዕቃችን እየተፈተሸ እያለ ከልመና ባላነሰ ሁኔታ እንደ ገና ነገረችኝ እኔ ግን ችላ አልኳት ፓስተሩን ሳገኘው ሴትየዋ ስለምትከፍልልን እዚያ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ ሆቴል ውስጥ እንደማናርፍ ነገርኩ በነገርኩት ቅር የተሰኘ መስሎ ስለ ታየኝ ችግሩ ምን እንደ ሆነ ጠየቅሁት ጆን ይህ ሽማግሌውንና ቤተ ሰቡን በጣም ያሳዝናቸዋል ያሰናክላቸዋል እነዚህ ሰዎች ለእናንተ ሲሉ ሆቴል ውስጥ ክፍሎች ይዘዋል ስለዚህ እነዚያ ክፍሎች በዚያ ሌሊት ማንም አይዛቸውም በማለት በግልጽ ነገረኝ ከዚያም ባለፈ እነርሱ ያዘጋጁልንን ባለ መቀበላችን ፓስተሩን ሳላሳዝነው እንዳልቀረሁም አስባለሁ በመጨረሻ እዚያ የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌ ሆቴል ውስጥ እንደምናርፍና የሴትዮዋን ግብዣ እንደማንቀበል ነገርነው የነበረኝን ዝንባሌ በተመለከተ ጌታ አስተማረኝ በሁኔታዬ ፓስተሩ መጐዳቱን አውቃለሁ የእኔን ሐሳብ መብት ብቻ መከተሌ ያንን ወንድም እንዳሰናከለው ማየት ቻልኩ ያ ደግሞ ኃጢአት ነው ይቅርታ እንዲያደርግልኝ ጠየቅሁት እርሱም ይቅርታ አደረገልኝ ያንን ትምህርት ድጋሚ እንደማልማር ተስፋ አደርጋለሁ መተናነጽን የሚመለከት ፈተና ሐዋርያው ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ በእግዚአብሔር ሐሳብ ውስጥ ያለውን ቁልጭ አድርጐ አስቀምጧል ስለዚህ ሰላም የሚገኝበትንና እርስ በርሳችንም የምንተናነጽበትን ማንኛውንም ጥረት እናድርግ ሮሜ በግል እኛ ካለን ነጻነት የተነሣ ሌሎች እንዲሰናከሉ አለማድረግ ዓላማችን ሊሆን ይገባል እያደረግን ወይም እየተናገርን ያለው የቅዱሳት መጻሕፍት ድጋፍ ያለው ሊሆን ይችላል ያም ቢሆን እንኳ የማደርገው ወይም የምናገረው ሌላውን ሰው ያንጻል ወይስ የእኔን መንገድ ብቻ ነው እየተከተልኩ ያለሁት። ኢየሱስ ሲናገር ግን የሚናገረው ትኩረት ሰጥተን እንድንቀበለው ነው እርሱ የሚነግረንን ሌሎች ባለ ሥልጣኖች ወይም በሕይወት ዘመናችን የሚገጥሙን ሰዎች የሚናገሩትን በምንመለከትበት መንገድ መውሰድ አንችልም አንድ ነገር ከተናገረ ያንን የተናገረው ከልቡ ወይም የምሩን ነው እኛ ታማኝ ባንሆንም እርሱ ታማኝ ነው ከእኛ ባሕል ወይም ማኅበረ ሰብ እጅግ በላቀ መልኩ እርሱ የሚመላለሰው በእውነትና በታማኝነት ደረጃ ነው ስለሆነም ኢየሱስ ይቅር ባትሉ ግን የሰማዩ አባታችሁ ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም ሲል ያንን የተናገረው ከልቡ ወይም የምሩን ነው አንድ ርምጃ ወደ ፊት ለመሄድ ያህል በወንጌሎቹ ውስጥ እርሱ ይህን የተናገረው አንዴ ብቻ ሳይሆን ብዙ ጊዜ ነው ይህ ማስጠንቀቂያ በጣም አስፈላጊ ለመሆኑ አጽንዖት እየሰጠ ነው የተናገረው ይህ አስመልክቶ በተለያየ ጊዜና ሁኔታ ውስጥ የተናገራቸው ጥቂቶችን እንይ እናንተ የበደሏችሁን ይቅር ብትሉሌ የሰማዩ አባታችሁ ደግሞ እናንተን ይቅር ይላችኃል ነገር ግን የሰዎችን ኃጢአት ይቅር የማትሉ ከሆነ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይልላችሁም ማቴዎስ እንደ ገና ይቅር በሉ ይቅር ትባላላችሁ ሉቃስ እንደ ገና በጌታ ጸሎት እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን የሚል እናነባለን ማቴዎስ የበደሉዋቸውን ሰዎች ይቅር በሚሉበት መንገድ እግዚአብሔርም እነርሱን ይቅር እንዲላቸው የሚፈልጉ ምን ያህል ክርስቲያኖች ሊሆኑ እንደሚችል ራሴን እጠይቃለሁ ያም ሆኖ ግን እነርሱ ራሳቸው ይቅር የሚባሉት በትክክል በዚህ መንገድ ነው በየቤተ ክርስቲያኖቻችን ይቅር አለመባባል በጣም ከመስፋፋቱ የተነሣ ይህን የኢየሱስን ቃል የምራችንን ወይም ከልባችን መውሰድ አንፈልግም እንዲህ ወይም እንዲያ መሆኑ ግን እውነቱን አይለውጠውም ይቅር የምንባለው ሌላውን ሰው ይቅር በምንልበት በምንፈታበትና ወደ ቀድሞ ሁኔታ በምንመልስበት መንገድ ነው በፊልፒንስ ስላለ አንድ አገልጋይ ያልተለመደ ዐይነት ምስክርነት ሰምቻለሁ በበፊቱ አገልግሎቱ እርሱን የሚያውቁ ወዳጆቼ ስለ ልምምዱ የሚናገር አንድ መጣጥፍ አሳይተውኛል በነበረው የንግድ ሥራ እጅግ እየተሳካለት ስለ ነበር ለሕይወቱ ከእግዚአብሔር የመጣውን ጥሪ ሰውየው መቀበል ተቸግሮ ነበር እጅግ በጣም ብዙ ገንዘብ እያገኘ ነበር አልታዘዝም ማለቱ የኃላ ኃላ ባስከተለው መዘዝ በከፍተኛ የልብ ሕመም በአስቸኳይ ወደ ሆስፒታል ተወሰደ እዚያው ኦፕራሲዮን የሚደረግበት ጠረሴዛ ላይ እያለ ይሞትና ራሱን የመንግሥተ ሰማይ ደጆች ላይ ያገኘዋል በዚያ ቦታ ኢየሱስ ቆሞ ነበር አለ መታዘዙን በተመለከተ ያናግረዋል ተጨማሪ ዕድሜ ከሰጠው በሙሉ ልቡ እንደሚሜያገለግለው ቃል በመግባት ሰውየው ጌታን ይለምነዋል ጌታም ልመናውን ይቀበላል ወደ አካሉ ከመመለሱ በፊት ጌታ ገሃነምን ያሳየዋል የሚስቱ እናት ገሃነም እሳት ነበልባል ውስጥ ስትቃጠል ይመለከታል ያንን በማየቱ በጣም ተገረመ ኃጢአተኛ ሰው የሚጸልየውን ጸሎት ጸልያ ነበር ክርስቲያን እንደ ሆነች ስትናገር ነበር ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን ትመጣ ነበር ወደ ገሃነም የተጣለችው ለምንድነው። ሌሎች ላይ የምንይዘው በደል እኛ እግዚአብሔር ላይ ከፈጸምነው በደል ጋር ሲነጻጸር ዶላርን ከ ቢሊዮን ዶላር ጋር የማነጻጸር ያህል ይሆናል ምናልባት አንድ ሰው ከባድ በደል አድርሶብን ይሆናል ሆኖም ያ እግዚአብሔር ላይ ከፈጸምነው በደል ጋር አይወዳደርም እናንተ ላይ የደረሰው በደል ማንም ላይ ደርሶ የማያውቅ ይመስላችሁ ይሆናል ሆኖም ኢየሱስ ላይ የደረሰው በደል ምን ያህል ከባድ እንደ ነበር መገንዘብ አትችሉም እርሱ ንጹሕ ነበር እንከን የሌለበት የታረደ በግ ነበር ይቅር ማለት የማይችል ሰው እርሱ ራሱ ይቅር የተባለለትን ታላቅ ዕዳ ዘንግቶአል ኢየሱስ ከዘላለም ሞትና ስቃይ እንዳዳናችሁ ከተገነዘባችሁ እናንተም ሌሎችን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ይቅር ትላላችሁ ምዕራፍ ዐሥራ ሦስት ላይ በዚህ ሁኔታ እንዴት መመላለስ እንደምንችል እንነጋገራለን ለዘላለም የእሳት ባሕር ውስጥ ከመጣል የከፋ ነገር የለም በዚያ ዕረፍት የለም እሳቱ አይጠፋም ትሉ አያንቀላፋም በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እግዚአብሔር ይቅር እስካለን ጊዜ ድረስ የእኛ መጨረሻ ያ ነበር ሃሌ ሉያ። ምናልባት እንደ ተታለላችሁ ተሰምቷችሁ ከሆነ የተደረገላችሁን ምሕረት ብዛት አልተረዳችሁትም ማለት ነው ለበቀል ቦታ የለም በአሮጌው ኪዳን መሠረት እኔ ላይ በደል ካደረሳችሁ ያንኑ እናንተ ላይ እንዳደርግ ሕጉ ድጋፍ ይሰጠኝ ነበር ማንኛውንም ዕዳ በወቅቱ መቀበል ክፉን በክፉ መመለስ ይፈቀድ ነበር ዘሌዋውያን ዘፀአት ይመ ሕጉ የማይገሠሥ ሥልጣን ነበረው በዚያ ዘመን እነርሱን ነጻ ለማውጣት ኢየሱስ ገና አልሞተም ነበር የአዲሱ ኪዳን አማኞችን በተመለከተ ግን የተነገረውን ተመልከቱ ዐይን ስለ ዐይን ጥርስ ስለ ጥርስ እንደ ተባለ ሰምታችኃል እኔ ግን አላችኃለሁ ክፉ አድራጊውን ሰው አትቃወሙት ነገር ግን ቀኝ ጉንጭህን ለሚመታህ ሌላውን ጉንጭህን ደግሞ አዙርለት አንድ ሰው እጀ ጠባብህን ሊወስድ ቢከስህ ካባህን ጨምረህ ስጠው አንድ ሰው አንድ ኪሎ ሜትር ተኩል የሚሜያህል ርቀት እንድትሄድ ቢያስገድድህ ዕጥፉን መንገድ አብረኸው ሂድ ለሚለምንህ ስጥ ከአንተም ሊበደር የሚሻውን ፊት አትንሣው ማቴዎስ ኢየሱስ ለበቀል ምንም ቦታ አልሰጠም እንዲያውም ሌላ በደል ሊደርስብን ቢችል እንኳ ያንን ለመቀበል ፈቃደኛ እስከ መሆን ድረስ ዝንባሌያችን እኛ ራሳችን ከመበቀል መታቀብ እንዳለብን ነው የተናገረው የደረሰብንን በደል በዐይነት ለመመለስ በፈለግን ጊዜ ሁሉ ራሳችንን ዳኝነት ወንበር ላይ ማስቀመጣችን ነው ማቴዎስ ላይ የተመለከትነው ይቅር ማለት ያልፈለገው አገልጋይ እንደ እርሱ አገልጋይ የነበረ ባልንጀራውን እስር ቤት ሲያስገባው ይህን ማድረጉ ነበር በምላሹ ይህ ይቅር ማለት ያልፈለገ አገልጋይ ለሚያሰቃዩት ተላልፎ ተሰጠ ዕዳውን በሙሉ ለመክፈል ቤተ ሰቡ መሸጥ ነበረባቸው እኛ ግን ጻድቅ ለሆነው ዳኛ ቦታና ዕድል መስጠት አለብን እርሱ በጽድቅ ዋጋ ይከፍላል በጽድቅ የሚበቀል እርሱ ብቻ ነው አንድ ጊዜ መሰናክልን በተመለከተ ቴምፓ ፍሎሪዳ ባለ አንድ ቤተ ክርስቲያን እያገለገልኩ እያለ አንዲት ሴት ወደ እኔ መጥታ የቀድሞ ባሏ ያደረሰባትን በደል ሁሉ ይቅር ብላው እንደ ነበር ነገረችኝ ሆኖም የበደልን እስራት ስለ መፍታት እያደረግሁ የነበረውን ንግግር ከሰማች በኃላ አሁንም ቢሆን ውስጧ ሰላም እንደሌላትና ጥሩ ያልሆነ ስሜት እንደሚሰማት ተረዳች አሁንም ቢሆን ገና ይቅር አላልሽውም አልኳት በጨዋነት እንዴ ይቅር ብየዋለሁ እንጂ አለች ኮስተር ብላ እንዲያውም እያለቀስኩ ነው ይቅር ያልኩት አልቅሰሸ ሊሆን ይችላል ግን ከበደል እስራት አልፈታሽውም እኔ እንደ ተሳሳትኩና እርሷ ግን ይቅር እንዳለችው አጥብቃ ተከራከረች ከእርሱ ምንም አልፈልግም ከበደል እስራትም ፈትቼዋለሁ እስቲ አንቺ ላይ ያደረገው ምን እንደ ነበር ንገሪኝ በማለት ጠየቅሁ እኔና ባሌ የአንድ ቤተ ክርስቲያን ፓስተሮች ነበርን እኔና ሦስት ወንዶች ልጆቻችንን ትቶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከነበረች አንዲት ታዋቂ ሴት ጋር ተወዳጀ ይህን ስትነግረኝ ዐይኖቿ እንባ አቅርረው ነበር እኔን በማግባቱ ከእግዚአብሔር ፈቃድ እንደ ወጣና አሁን የተወዳጃትን ሴት ማግባቱ ግን ትክክለኛ የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ነገረኝ ከእኔ የበለጠ በጣም ተባባሪው በመሆንዋ እርሷ ለአገልግሎቱ ታላቅ ቅርስ እንደ ሆነችና እኔ ግን ዕንቅፋት እንደ ሆንኩበት ነገረኝ ነቃፊና ተቺ መሆኔን ነገረኝ ለትዳራችን መፍረስ ሙሉ በሙሉ ተጠያቂዋ እኔ እንደ ሆንኩ ነገረኝ ከዚያ በኃላ ተመልሶ አልመጣም አንድ በደል እንኳ ማድረሱንም አልተቀበለም ይህ ሰው ከባድ ስሕተት መፈጸሙና ሚስትና ልጆቹን በጣም መጉዳቱ ግልጽ ነው በፈጸመው በደል በጣም ተጐድታለች ለበደሉ ተመጣጣኝ ክፍያ እንዲያደርግ እየጠበቀች ነበር ከእርሱ እየጠበቀች የነበረው የፍቺ ገንዘብ ወይም ለልጆቿ ማሳደጊያ እንዲሰጣት አልነበረም አዲሱ ባሏ ይህን ሁሉ እያደረገላት ነበር እንዲከፍላት የምትጠብቀው ክፍያ እርሱ በደል መፈጸሙንና እርሷ ግን ትክክል እንደ ነበረች እንዲያምን ብቻ ነበር ወደ አንቺ መጥቶ በደል ማድረሱንና ጥፋቱ የእርሱ እንጂ የአንቺ አለመሆኑን ካልተናገረ ከዚያም ይቅር እንድትዬው ካልጠየቀ ይቅር ልትዩው አልፈለግሽም ያለበትን ዕዳ እንዲከፍልሽ እየጠበቅሽ ነው እስረኛ ያደረገሸ ይህ ያልተከፈለሽ ዕዳ ነው በማለት እውነቱን ነገርኳት ወደ እርሱ መጥተን እኛ ተሳስተናል አንተ ግን ትክክል ነህ ስለዚህ ይቅርታ አድርግልን በማለት እስክንጠይቀው ድረስ ኢየሱስ ቢጠብቅ ኖሮ መስቀል ላይ የሞተ ጊዜ ይቅር አይለንም ነበር መስቀል ላይ ተሰቅሎ እያለ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው በማለት ጮኸ ሉቃስ ወደ እርሱ መጥተን እርሱን እንደ በደልን ከመናዘዛችን በፊት ነበር እርሱ ይቅር ያለን ሐዋርያው ጳውሎስም ጌታ ይቅር እንዳላችሁ እናንተም ሌላውን ይቅር በሉ ቄላስይስ እንደ ገና እግዚአብሔር በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተም ይቅር ተባባሉ እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ሩኀሩኖች ሁኑ በማለት ይመክረናል ኤፌሶን ታዲያ እኔ በድያለሁ አንቺ ግን ትክክል ነሽ። መለያየትና መከፋፈልን የምትዘሩ ከሆነ ያንኑ እንደምታጭዱ ልብ አድርጉ አቤሴሎም ላይ የደረሰውና በዘመናችን ባሉ አገልግሎቶች ላይ እየሆነ ያለው ጊዜ የሚጠይቅ ሂደት ነው ብዙ ጊዜ ልባችን ውስጥ ቅርታ መራራነት ወይም መሰናክል መግባቱን እንኳ ላናውቀው እንችላለን በማደግ ላይ እያለ የመራራነት ሥር የሚታወቀው በጣም አልፎ አልፎ ነው በኃላ ግን ሙሉ ዕድገት ደረጃ ላይ ይደርሳል በብዛትም ሆነ በጥንካሬ ይበረታል የዕብራውያን ጸሐፊ እንደሚመክረን መራራ ሥር በቅሎ ችግር እንዳያስከትልና ብዙዎችን እንዳይበክል መጠንቀቅ አለብን ዕብራውያን ልባችንን መመርመርና ለእግዚአብሔር እርምት ሕይወታችንን መክፈት አለብን ምክንያቱም የልባችንን ሐሳብና ዝንባሌ መለየት የሚችል የእርሱ ቃል ብቻ ነው መንፈስ ቅዱስ ለሰው ልብ በመናገር ይወቅሳል በደልን ያሳያል የእርሱን ወቀሳ ችላ በማለት እርሱን ማሳዘን የለብንም እንዲህ ካደረግን በእግዚአብሔር ፊት ንስሐ እንግባ ለእርሱ እርምት ልባችንን እንክፈት አንድ ጊዜ አንድ አገልጋይ ቀደም ሲል አድርጐ የነበረውን ነገር አስመልክቶ ተግባሩ ከአቤሴሎም ወይም ከዳዊት ማንኛውን እንደሚመስል ጠይቆኝ ነበር ይህ ሰው ከተማው ውስጥ ለነበረ አንድ ፓስተር ረዳት ሆኖ ይሠራ ነበር በኃላ ግን ፓስተሩ ከሥራው ያባርረዋል የእግዚአብሔር እጅ ከእርሱ ጋር መሆኑ በግልጽ ይታይ ነበር ዋናው ፓስተር ይህን ወጣት ይመቀኘውና ይፈራው ነበር ከአንድ ዓመት በኃላ ያ የተባረረ አገልጋይ በዚያው ከተማ ሌላ ሰፈር ቤተ ክርስቲያን እንዲመሠርት የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ያምናል ያንንም ያደርጋል ትቶት ከመጣው ቤተ ክርስቲያን አንዳንድ ሰዎች መጥተው ከእርሱ ጋር ሆኑ አቤሴሎም እንዳደረገው እርሱም እንዳያደርግ ይፈልግ ስለ ነበር በነገሩ ስጋት ገብቶት ነበር ይሁን እንጂ ይህ ሰው በቀድሞ ፓስተሩ ላይ ጥላቻ ወይም ምሬት አልነበረበትም አዲሱን ቤተ ክርስቲያን የመሠረተው የቀድሞውን ቤተ ክርስቲያንን ለመጋፋት አልነበረም እንደዚያ እንዲያደርግ ከእግዚአብሔር ምሪት በመቀበሉ ብቻ ነበር በአቤሴሎምና በዳዊት መካከል የነበረውን ልዩነት አሳየሁት መሪው የነበረው ሰው ሳይ ካደረበት ጥላቻ የተነሣ አቤሴሎም የሌሎችን ልብ አሸፈተ ምንም እንኳ ሳኦል እርሱን እያሳደደው ቢሆንም ለሳኦል ታማኝ እንዲሆኑለት ዳዊት ሌሎችን ሲመክር ነበር አቤሴሎም ሰዎችን ለራሱ ወሰደ ዳዊት በነበሩበት ተዋቸው ታዲያ አንተ ሰዎቹን ባሉበት ቦታ ትተህ ነው የሄድከው አይደል። የሚል ይሆን ነበር ሆኖም ለራሴ መከላከል የእነርሱን ተበድለናል የማለት እልህ የበለጠ ያቀጣጥለዋል እንጂ ምንም አይጠቅምም ሰላም የመፍጠር መንገድም አይደለም ለራሳችንና ለመብታችን መከራከር እውነተኛ ሰላም አያመጣም ከዚያ ይልቅ መናገር የሚፈልጉትን ሁሉ ተናግረው እስኪጨርሱ ድረስ ማድመጥ እንጂ እኔ ምንም መናገር እንደማይገባኝ ተረድቻለሁ በተናገሩት ነገር ባልስማማ እንኳ የተናገሩትን እንደማከብርና እኔ ግን ልቤንና ዝንባሌዬን እንደምመረምር እንዲያውቁ አደርጋለሁ ከዚያም እነርሱን በመጉዳቴ ማዘኔን እነግራቸዋለሁ ሌላ ጊዜ ደግሞ እኔን በተመለከተ የተናገሩት ትክክል ሆኖ ይገኛል እንዲህ ከሆነ አዎን ትክክል ናችሁ ይቅርታ አድርጉልኝ እላቸዋለሁ አሁንም ቢሆን ዕርቅን ለማውረድ ሲባል ራስን ዝቅ ማድረግ ተገቢ መሆኑን መገንዘብ አለብን ማለት ነው ምናልባትም ቀጥሎ ያለውን ኢየሱስ የተናገረው በዚህ ምክንያት ሊሆን ይችላል የከሰሰህ ባላጋራህ እንዳያስፈርድብህ ዳኛውም ለአሳሪ አሳልፎ እንዳይሰጥህ በወህኒም እንዳትጣል በመንገድ ላይ ሳለህ ከባላጋራህ ጋር ፈጥነህ ተስማማ እውነት እልሃለሁ ካስፈረደብህ ግን የመጨረሻዋን ሳንቲም እስክትከፍል ድረስ ከዚያ አትወጣም ማቴዎስ ትዕቢት እውነት ቢሆን እንኳ ራሱን ይከላከላል ትሕትና ግን በመስማማት አዎን ልክ ነህ እንዲህ በማድረጌ አጥፍቻለሁ እባክህን ይቅርታ አድርግልኝ ይላል ከሰማይ የሆነችው ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት በኃላም ሰላም ወዳድ ታጋሽ እሺ ባይ ምሕረትና መልካም ፍሬ የሞላባት አድልዎና ግብዝነት የሌለባት ናት ያዕቆብ ከእግዚአብሔር የሆነ ጥበብ እሺ ባይና ሰላም ወዳድ ነው በግል ከሰዎች ጋር የሚኖረውን ግጭት በተመለከተ አንገተ ደንዳና ወይም ግትር አይደለም በመንፈሳዊ ጥበብ የሚመራ ሰው አጥፍቻለሁ ማለትን ወይም እውነትን እስካልተጻረረ ድረስ ሌሎች ከሚያቀርቡት ሐሳብ መለየትን አይፈራም የበደላችሁን ሰው መቅረብ እስከ አሁን ወንድማችንን ስንበድል ወይም ስናሰናክል ምን ማድረግ እንዳለብን ተመልክተናል አሁን ደግሞ ወንድማችን እኛን ሲበድለን ወይም ሲያሰናክለን ምን ማድረግ እንዳለብን እንመለከታለን ወንድምህ ቢበድልህ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻ ሆናችሁ ጥፋቱን ንገረው ቢሰማህ ወንድምህን እንደ ገና የራስህ ታደርገዋለህ ማቴዎስ ብዙዎች ይህን ጥቅስ የሚጠቀሙበት ኢየሱስ ማስተላለፍ ከፈለገው መልእክት በተለየ ዝንባሌ ነው በደል ደርሶባቸው ከሆነ ወደ በዳዩ ወገን ሄደው በበቀልና በቁጣ መንፈስ ይጋፈጡታል የበደላቸው ሰው ላይ ለመፍረድ ይህን ጥቅስ እንደ ድጋፍ ይወስዱታል ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች ኢየሱስ ይህን የተናገረበትን ዓላማ ስተዋል ዓላማው ፍርድ ሳይሆን ዕርቅ ነው ወንድማችን ምን ያህል እንደ በደለንና በዚህም ምክንያት ሊፈረድበት እንደሚገባ እንድንነግረው አይደለም ኢየሱስ የፈለገው ከእርሱ ጋር የነበረን ግንኙነት እንዳይታደስ ዕንቅፋት የሆነ ነገርን ለማስወገድ ነው ወደ እርሱ መሄድ ያለብን ይህ እግዚአብሔር እኛን ወደ ራሱ ከሚያመጣበት ሁኔታ ጋር ይመሳሰላል እኛ እግዚአብሔርን በድለናል ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞተ ይህም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያሳያል ሮሜ ታዲያ እኛ ለራሳችን መከራከርን ለመተውና ከበደለን ሰው ጋር ሰላም ለመፍጠር ሲባል ለትዕቢት ለመሞት ፈቃደኞች ነን። ብለህ ራስህን ስትጠይቅ ይቆጭሃል እውነትን ሳታመቻምች የሚቻልህን ሁሉ ማድረግህንና ያንን ያደረግኸው ሌላ አማራጭ ስላልነበረህ መሆኑን ማስረገጥ መልካም ነው አለ ስለ ምክሩ ያንን ወዳጄን በጣም ነው የማመስግነው ምክሩ የእግዚአብሔር ጥበብ እንዳለበትም እረዳለሁ ኢየሱስ እንዲህ ማለቱን አስታውሱ ሰላምን የሚያወርዱ ብፁዓን ናቸው የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉና ማቴዎስ ምንም ግጭት እንዳይኖር የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው አይደለም ያለው ምንም ግጭት እንዳይኖር የሚፈልግ ሰው እውነትን በማመቻመች እንኳ ቢሆን ሰላም እንዲኖር በማሰብ ፊት ለፊት መጋፈጥ አይፈልግም ሆኖም ይህ እውነተኛ ሰላም አይደለም ዘለቄታ የሌለው አርቲፊሻልና አስመሳይ ሰላም ነው ሰላም የሚያወርድ ሰው ግን የሚገኘው ዕርቅ ዘላቂነት እንዲኖረው በፍቅር ሄዶ እውነትን ይናገራል ይህ ሰው አርቲፊሻልና አስመሳይ ወዳጅነት እንዲኖር አይፈልግም ግልጽነትን እውነትንና ፍቅርን ነው የሚፈልገው የሽንገላ ፈገግታ በማሳየት መበደሉን አይደብቅም ዘላቂነት ባለው ደፋር ፍቅር መሠረት ላይ ሰላምን ይገነባል እግዚአብሔርም ለሰው ልጆች እንዲሁ ነው እርሱ ማንም እንዲጠፋ አይፈልግም ይሁን እንጂ ከእርሱ ጋር ያለንን ግንኙነት በተመለከተ እውነትን አያመቻምዎችም እንዲሁ ላይ ላዩን በሚደረግ ስምምነት ሳይሆን በእውነተኛ መሰጠት ዕርቅ እንዲኖር ነው የሚፈልገው ይህ የትኛውም የክፋት ኃይል መበጠስ በማይችልበት ሁኔታ የፍቅርን ማሰሪያ ያጠነክራል እርሱ ለእኛ ሕይወቱን ሰጥቶናል እኛም እንደዚያ ማድረግ ብቻ ነው የሚጠበቅብን እዚህ ላይ አንኳሩ እውነት የእግዚአብሔር ፍቅር መሆኑን ልብ አድርጉ የእግዚአብሔር ፍቅር አይጠፋም አይደበዝዝም ማለቂያ ማብቂያም የለውም የራሱን አይፈልግም በቀላሉ አይበሳጭም ቆሮንቶስ የእግዚአብሔር ፍቅር ማንኛውንም ዐይነት ኃጢአት እንደሚያሸንፍ ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ጽፎአል ፍቅራችሁ በጥልቅ ዕውቀትና በማስተዋል ሁሉ በዝቶ እንዲትረፈረፍ እጸልያለሁ ይኸውም ከሁሉ የሚሻለውን ለይታችሁ እንድታውቁ እስከ ክርስቶስም ቀን ድረስ ንጹሐንና ነቀፋ የሌለባችሁ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሚገኘው የጽድቅ ፍሬ እንድትሞሉ ነው ፊልጵስዩስ ከመሰናክል ወጥመድ ነጻ በመሆን ረገድ ቁልፉ የእግዚአብሔር ፍቅር ነው ይህ ፍቅር ሞልቶ የተትረፈረፈ ፍቅር በየጊዜው ልባችን ውስጥ እያደገና እየጠነከረ የሚሄድ ፍቅር መሆን አለበት በዚህ ዘመን ማኅበረ ሰባችን ውስጥ ያሉ ብዙዎች መናገር እንጂ መሥራት በማይፈልግ ላይ ላዩን በሆነ ፍቅር ተታልለዋል ከመሰናክል የሚጠብቀን ፍቅር ሌላው ቀርቶ ለጠላቱ እንኳ መልካም እንዲሆን ያለ ስስት ራሱን ይሰጣል በዚህ ዐይነቱ ፍቅር ስንመላለስ በሰይጣን ሽንገላ አንጠመድም መደምደሚያ ርምጃ መውሰድ ህን መጽሐፍ በማንበባችሁ ባለፈው ጊዜ ወይም በአሁኑ ጊዜ ባላችሁ ግንኙነት አንዳች ነገር የያዛችሁባቸው ሰዎችን የእግዚአብሔር መንፈስ አሳስቦአችሁ ይሆናል እንደዚያ ከሆነ የሚከተለውን አጭር የመፈታት ጸሎት አብረን እንድንጸልይ እጠይቃችኃለሁ ሆኖም ከመጸለያችሁ በፊት ከእናንተ ጋር አብሮ ወዳለፈው ጊዜ ልምምምችሁ እንዲመለስና አንዳች ነገር የያዛችሁባቸው ሰዎችን ወደ ልባችሁ እንዲያመጣ መንፈስ ቅዱስን ጠይቁት እነዚያ ሰዎች እነማን እንደ ሆኑ እያሳያችሁ እያለ በፊቱ ፀጥ በሉ በመሠረቱ በቦታው የሌለ ነገርን መፈለግ የለባችሁም መጠራጠር በማትችሉበት ሁኔታ እግዚአብሔር በግልጽ ወደ ልባችሁ ያመጣቸዋል እንደዚያ በሚያደርግበት ጊዜ ሕመም ሊኖር እንደሚችል መዘንጋት የለባችሁም ያም ቢሆን አትፍሩ እናንተን ለማጽናናት እርሱ ሁሌም ከጐናችሁ ነው ያለው እነዚያ በደል ያደረሱባችሁን ሰዎች ከወቀሳና ከበደል እየፈታችኃቸው እያለ እያንዳንዱን በአእምሮአችሁ ውስጥ ሳሉዋቸው እያንዳንዱን ሰው በግል ይቅር በሉሌ ለእናንተ ያለባቸውን ዕዳ ሰርዙ ከዚያ ይህን ጸልዩ ሆኖም በእነዚህ ቃሎች መወሰን የለባችሁም ይህን ጸሎት እንደ መመሪያ ተጠቀሙበት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራት አለባችሁ ያሦ ዎሪዐፀ ደለ ሯደረራታሃኝ ሪሪዎቻ ይሪቀረ ፅ ማሰታ ሥ ቂፀ ኃዉታሦ ማድረ ዕዲዖታዕ ሰም ዳፇፅያሰሥ ደ ዕ ዳሐሥ ይሳ ሪቀርታም ዳጨይቃሰታሥ ጂለታ ውጪ ይፇቀረሮ ልጳተሮሦሮው ደማሳፇሦጳም ውቃለታሥ ኃለሐደዖ ለደሾ ይ ያሪመሯያጀ ዕም ሪሬጩምሩ ጳዲያፉ ያጳዕራሦ ፉፍቋ ዕልፊጩ ሪቀረ ማሐፖ ጳፈልጋሰሥ ዳዕ ሪፅ ሪኗረራታሦ ደቋጂ ያሖ ያኖዲጴዖታዕ ደም ሪታሥቻ ለኛሮራሰሥ ዖዳኋሪ ቋ ሪናዎም ሊሪፀደሐም ዳዕ ፋሪ ያዖፈፊጸሙታፖቓ ኃዉዳሦ ይቅረ ዖፆጎሥ ጭመሟ ጸፀ ረታ ዖሪደሖሥፖ ዳ ይፇቀረ ጳድታል ታሥይ ጴጊዖሖዕ ለፉታሦ ድ ጠያዖፇ ታሐ ይም ዳዕ ሪ ኃዉዳፖሦፖ ፉሪጽሙ ሥንችቻ ፈሪ ያጎላፉ ሪቀርረታ መማ ጳሷሏያያቋሥታ። ሃቀ ሐቋማጭድሪሃናኖ ይቀርታ መጠያቅ ዱያጎሥምረሃ ዳህሠጨረ ሐም ቀን መንፈሳዊ ከርታቶች ዖሂቋሌረ ያፇያባው ፍፖሥይ ይ ሀ ዖጎው ታሃሮ ያማድሪግና ዳጳዳሂዳሠሬረ ዖፇፃው ለሆሪም ጳደ ጳረታ ሪ ያማሃ ዳሂዳጩሌሪ ይጠዝፇንኝ ጎቻው ዊም ሪሥጅ ያኗ ቃለ ሥዳቻሥፖ ኦታለ ይ ሐዴ ዳጂያደረታያ ቀም ጳኋጂፈሦሮደጎፖውምሥ ዓሙጴዔጳ ፁፖ ባጽ አንብብ ሳኦልና በዳዊት መካከል በነበረው ግንኙነት እግዚአብሔር የዳዊትን ልብ እየፈተነ ነበር ሳሙኤል ከሳኦል በኃላ የሚቀበለውን መንግሥት ለማጽናት ይገድለው እንደ ሆነ ወይም እርሱ ራሱ መንግሥቱን ለዘላለም እንዲያጸናለት ይጠብቅ እንደ ሆነ ግልጽ እንዲሆን እግዚአብሔር ፈልጓል የመፍረድና የመበቀል መብት ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው ሮሜ ላይ ወዳጆቼ ሆይ ለእግዚአብሔር ቁጣ ፈንታ ስጡ እንጂ አትበቀሉ በቀል የእኔ ነው እኔ ብድራትን እመልሳለሁ የሚል እናነባለን የእግዚአብሔርን ሥራ ድርሻ እኛ መውሰድ የለብንም ትክክል የሆነ ነገርን በተሳሳተ መንገድ ማድረግ ተገቢ አይደለም አዎን ሳኦል ሊፈረድበትና ሊቀጣ ይገባው ነበር ያን ማድረግ የነበረበት ግን ዳዊት አይደለም ዳፇጨረ ያመጠያያፇዎ ይለቀ ሃ ራዕሃ ዲሯ ዖታያፇልያታ ሄይ ዳጋ ሁይታውኖ ውጩጨኃ ግሰዎ እግዚአብሔር ሰዎችን ከባድ ስሕተት በሚፈጽሙ ከዚያም አልፎ ዐመፀኛ በሆኑ መሪዎች ሥር የሚያኖረው ለምንድነውወ በማለት ብዙዎች ይጠይቃሉ እንደ ምሳሌ ሳሙኤል ይመ ገና ሕፃን እያለ እግዚአብሔር ሳሙኤልን ብልሹ በነበረው ዔሊ ሥር አኑሮት ነበር እዚያ በነበረ ጊዜ ሳሙኤል በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር መደገፍንና መታመንን በእርሱም መመራትን ተማረ በኃላም ብልሹ መሪዎቹን እግዚአብሔር ራሱ ቀጣቸው በእርሱ ፍቅርና በሚያጠራ እሳቱ ቅርጽና መልክ እንድንይዝ አንዳንዴ እግዚአብሔር አዳጋችና ከባድ ሁኔታዎች ውስጥ ያኖረናል በደረሰብን በደል ተማርረን ጥለን ብንሄድ እግዚአብሔር ለእኛ ያዘጋጀውን ሳንቀበል እንቀራለን ይልቁን በበደል ላይ በደል እንጨምራለን በደል የደረሰባቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ የአጸፋ ምላሽ ይሰጣሉ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ባይሆንም ለሰው ትክክል መስሎ የሚታይ ነገር ያደርጋሉ እንደ እውነቱ ከሆነ በታዛዥነት ለእግዚአብሔር ምላሽ እንድንሰጥ እንጂ ለአዳጋች ሰዎች ወይም ሁኔታዎች የአጸፋ ምላሽ እንድንሰጥ አይደለም የተጠራነው በእርሱ ፍቅርና በሚያጠራ እሳቱ ቅርጽና መልክ እንድንይዝ አንዳንዴ እግዚአብሔር አዳጋችና ከባድ ሁኔታዎች ውስጥ ያኖረናል በደል ሲደርስብን ወይም ደስ የማይል ሁኔታ ሲገጥመን ከእግዚአብሔር እፎይታ የሚሰጥ ቃል እንፈልጋለን ይሁን እንጂ እንዲህ ያሉ ነገሮች እንዲደርሱብን እግዚአብሔር የፈቀደው በሳሎች ሊያደርገን ሊያጠራንና ሊያበረታን እንጂ ሊያጠፋን አይደለም።